All posts by Admin

የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስን በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

የዘንድሮዉ የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስ በደመቀ ሁኔታ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይከበራል:: መጥተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

መቼ? / When?
ማነክሰኞ ነሐሴ 16, 2015 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ
Tuesday August 22, 2023 from 2:00 pm

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ / Click Here to Follow Us On Facebook

የደብረ ታቦር ክብረ በዓልን በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

መቼ? / When?
ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ
Saturday August 19, 2023 from 4:00 pm

የዚህ ዓመት የደብረ ታቦር ክብረ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 (Saturday August 19, 2023) ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ዝግጅትይከበራል። እርስዎም መጥተው የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ የቤዛ ኩሉ የሰንበት ትምህርት ቤት ጥሪውን ያቀርባል።

ደብረ ታቦር (Transfiguration- Debre Tabor)

ነሐሴንና ጳጉሜን የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የደብራችን አባላት የእንቅስቃሴ ወሮች እንዲሆኑ ስለማቀድ

በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም.ን መገባደጃ በመንተራስ በቀሪዎቹ የነሐሴና ጳጉሜ ወሮች የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የቤተክርስቲያን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብሮች እንዲታቀዱ የአስተዳደር ቦርዱ ወስኖ የሚከተሉት መርኅግብሮች እንዲከናወኑ ይሆናል:: አዲስ የቤተክርስቲያን አባል ማለት በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም የደብራችን አባል የሆኑ ማለት ነው::

የአዲስ አባላት የትውውቅ መርኅግብር:-

  1. እሁድ እሁድ ከቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ እታች አዳራሽ ውስጥ አዲስ የቤተክርስቲያን አባሎቻችንን የእንኳን የደብራችን አባል ሆናችሁ በማለት የካህናት የአስተዳደር ቦርድ እና የአባላት ማኅበራት ተወካዮች ጋር ትዉዉቅ ይደረጋል::
  2. የእዲስ አባላት ስም ዝርርዝም እታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው ቴሌቪዥን ስኪሪን ላይ ይተላለፋል::
  3. የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ ላልወስዱ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  4. በእለቱም ለ ዲስ አባላት ቡና ሻይና ዳቦ ካለ ይቀርባል::

የነባር የደብራችን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብር:-

  1. ነባር የቤተክርስቲያን አባሎች እሁድ እሁድ አታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው የቦርድ አባላት የጠረጴዛ ቢሮ ድረስ በመሄድ የአባላት መዝገብ ላይ ያለው አድራሻችሁ ስልክ ቁጥራችሁና ኢሜል ትክክል እንደሆነ እንድታረጋግጡልን በአክብሮት እንጠይቃለን::
  2. የደብራችን አባልነት አዲስ መታወቂያ ካርድ ያላወጡ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  3. የየደብራችን አባልነት የወርሀዊ መዋጮአችሁ መጠናቀቁን የቦርድ አባላትን መጠየቅና ውዝፍ ካለ በወቅቱ እንዲጠናቀቅ መሞከር
  4. የደብራችን አባል ያልህኑ ዘመዶች ጏደኞች እና ወዳጆችን የቤተክርስቲያኗ አባል እንዲሆኑ ማነቃቃትና ማበረታታት
  5. የቤተክርስቲያናችን የመረዳጃ ማህበር አባል ለመሆን መሞከር
  6. ገቢው ለአዲስ ቤ.ክ. ማስሪያ የሚውል የበጎፍቃድ ስራ አገልግሎት ላይ ለመሳተፍ ከፕሮግራሙ እስተባባሪ ከዶ/ር አሻግሬ መረጃ መጠየቅ

መርኅግብሮቹ ከመጪው እሁድ የቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ ለአምስት ተከታታይ እሁዶች የምንከታተላቸው ይሆናል:: ቀኖቹም ነሐሴ7(Sug 13), ነሐሴ14(Aug 20), ነሐሴ21(Aug 27), ነሐሴ28(Sep 3), ጳጉሜ5(Sep 10) ናቸው::

ያቀድናቸውና ያሰብናቸው እንዲሳኩ ውድ የደብራችን ነባርና አዲስ የቤተክርስቲያን አባላት ከምንጊዜውም በበለጠ ሁኔታ የሰበካ ጉባዔውን እንድትተባበሩት በትህትና እንጠይቃለን:: በፅሁፍም ሆነ የመረጡትን የሰበካ ጉባዔ አባል በግል በመቅረብ አዳዲስ የአሰራር ሃሳቦችን እንድታካፍሉን ይሁን::

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች እንኳን ደስ ያላችሁ ! / Congratulations to 2023 Grads & Families!

“ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ” መዝ.118:26

በዘንድሮው የ2023 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍልን እና የከፍተኛ ትምህርትን ላጠናቀቁ የቤተክርስቲያናችን ወጣቶች የእንኳን ደስ ያላችሁ የምስክር ወረቀት ቤተክርስቲያናችን ባለፈው እሁድ ሐምሌ 30 (Aug 6, 2023) አበርክታለች:: የሚቀጥለው የትምህርትና የመደበኛ ስራ ዘመናቸውም የተቃና እንዲሆንላቸውም ከእግዚያብሔር ቤት ተመርቀዋል::

Congratulations to 2023 grads and families. Graduates were handed out congratulating certificates by our church during the Sunday church services on Aug 6, 2023.

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ !

ጾመ ፍልሰታ / የነሐሴ ቅዳሴ አገልግሎት ቀኖች እና የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች / DSMA Calendar of Activities in August 2023

ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 (Aug 7 – Aug 22) ጾመ ፍልሰታ ሙሉ ቅዳሴ አለ

የንግሥ በአላት ፀሎት እና ቅዳሴ አገልግሎቶች / Annual Holidays and Celebrations with Liturgical services ነሐሴ 13 (Aug 19) – ደብረ ታቦር (Transfiguration- Debre Tabor)
ነሐሴ 16 (Aug 22) የነሐሴ ኪዳነምህረት ንግስ (The assumption of Virgin Mary)


የአዘቦት ቅዳሴ አገልግሎት ቀኖች ( Covenant prayer services)
ነሐሴ 12, ነሐሴ 19, ነሐሴ 21, ነሐሴ 27 (Aug 18, Aug 25, Aug 27, Sep 2)

የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች / Volunteer Services dates for fundraising
. At the US Bank Stadium : Aug, 12, Aug 19 & Aug 26
. At the State Fair Parking : Aug 26 & Aug 27, Sep 2 to Sep 4

በኦገስት እስከ 14 የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች አሉ / 14 volunteer days in August. Let’s go DSMA!

ዲሱን የቤተክርስቲያናችንን ሕንፃ ለመገንባት የሚያስፈልገንን ገንዘብ ለማሰባሰብ ከኪሳችን ከምናዋጣው በተጨማሪ ነፃ የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በስታድየም እየሰጠን እንገኛለን:: የእናንተን ቀና ትብብር በመተማመንና ተስፋ በማድረግ በዩኤስ ባንክ ስታድየም በተጨማሪ ሌላ አማራጭዎችን በመፈለግ ላይ እንገኛለን::

በዚህም ፍለጋ ሂደት በመጭው የሚኔሶታ ስቴት ፌር (MINNESOTA STATE FAIR) ከ THURSDAY, AUGUST 24, 2023 – MONDAY, SEPTEMBER 4, 2023 ለ12 ቀናት በመስራት ገንዘብ ለመሰሰብ አጋጣሚው አለን::
ስራው:- ፓርኪንግ ጥበቃ
ሰዓት :- 6 ኤኤም እስከ 8 ፒኤም
የሰው ቁጥር:- 5 ወይም 7 በአንድ ፓርኪንግ ሜዳ
የፓርኪንግ ሜዳዎች ቁጥር:- 5

እባክዎን ሚኔሶታ ስቴት ፌር የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት July 23, 2023 ይመዝገቡ!

Thank you Dr Ashagre for diversifying our volunteer for church funds opportunity to include work at state fair events. There are 14 volunteer dates in August. Three days at US Bank Stadium (Aug 12, Aug 19 and Aug 26) and 12 days at MN State Fair (Aug 24 – Sept 4). As you would surmise Identifying and Coordinating the volunteer pool for the state fair events is the most pressing at the moment as we would need to know the number of volunteers by EOD Sunday July 23.

We are kindly asking all of you to consider registering as an individual or as a group for the state fair events from Aug 24 to Sept 4. There will be 7 weekdays and 5 weekends and public holidays during the event. The math is clear. The more days and/or the more parking lots we staff the more funds we will generate for our church. Let’s go DSMA!

ስለሆነም በኦገስት እስከ 14 የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች አሉ: እነሱም

  1. Saturday, Aug 12, 2023, Ed Sheeran Concert
  2. Saturday, 19 Aug 2023 | Tennessee Titans at Minnesota Vikings . Game starts at 7:00 pm | volunteer check in at 3 pm.
  3. Thursday, 24 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  4. Friday, 25 Aug 2023 | State Fair Parking Lots
  5. Saturday, 26 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  6. Saturday, 26 Aug 2023 | Arizona Cardinals at Minnesota Vikings | Game start at noon | volunteer check in at 8 am
  7. Sunday, 27 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  8. Monday, 28 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  9. Tuesday, 29 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  10. Wednesday, 30 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  11. Thursday, 31 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  12. Friday, 01 Sept 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  13. Saturday, 02 Sep 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  14. Monday, 03 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  15. Tuesday, 04 Sept 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots

July 29, 2023 ልናደርገው የነበረው የገንዘብ ማሰባስብ እቅዳችንን ለመሰረዝ ተገደናል / BCC FUNDRAISER AT THE ETHIOPIA DAY IN MINNESOTA IS CANCELLED

የቤተክርስትያናችን የህንጻ ግንባታ ኮሚቴ አባላት July 29, 2023 በሚኒሶታ የኢትዮጵያ ቀን አከባበር ሜዳ ላይ ተገኝተዉ ምግብ መጠጥ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን በመቨጥ ለአዲስ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ግንባታ የሚዉል ገንዘብ እንደሚያሰባስቡና እናንተም እንድትጐቦኟቸው የሚል ማስተወቂያ በዚህ ገጽ ላይ መለጠፋችን ይታወሳል::

ነገር ግን ከዚህ በፊት ባልታዩ ምክኒያቶች ብቻ በሚኒሶታ የኢትዮጵያ ቀን አከባበር ሜዳ ላይ ተገኝተን ልናደርገው የነበረው የገንዘብ ማሰባስብ እቅዳችንን ለመሰረዝ ተገደናል:: ከይቅርታ ጋር!

Due to unforeseen circumstances, the upcoming BCC grill fundraiser event at the Minnesota Ethiopia Day celebration on July 29, 2023 is cancelled. Please accept our apology.

የዘንድሮዉ ዓመት የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ እና የዋዜማ አገልግሎት፣ ሐምሌ 15 እና ሐምሌ 16, 2015 በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይከበራል:: The annual Hamle Gebriel celebration will be on July 22 & July 23, 2023.

የዋዜማዉ አገልግሎት በመጪዉ ቅዳሜ ሐምሌ 15, 2015 (Saturday July 22, 2023) ከ 4pm ጀምሮ ይከበራል::

የማኅሌት አገልግሎት በመጪዉ እሁድ ሐምሌ 16, 2015 (Sunday July 23, 2023) ከንጋቱ 2 am ጀምሮ ይሰጣል::

ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የቅዱስ ገብርኤልን በረከት ይካፈሉ ዘንድ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN
55406

የዘንድሮዉ ዓመት የ5,000 ሜትር ርቀት ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በደመቀ መልኩ በሰላም ተጠናቀቀ / This year’s 5K run and walk was a successful event

የሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት እና ቤተሰቦቻቸው ቅዳሜ ሰኔ 24 2015 (July 1st, 2023) በፌለን መናፈሻ ውስጥ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀውን የ5,000 ሜትር ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በደመቀ መልኩ ተሳትፈው መርኃ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል::

Members, families and friends of Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota came out in large numbers at the 9th annual 5K run and walk on July 1st, 2023 at Phalen Park, St Paul, Minnesota.

በእለቱም አሸናፊዎች የተዘጋጀላቸውን ሜዳልያና ምስክር ወረቀት ከደብራችን አስተዳዳሪ ከመልአከ ጽዮን ቀሲስ አዲስ ሞላው እና ከመርኃ ግብሩ አዘጋጆች ተቀብለዋል::
5K run and walk winners were recognized with medals and certificates from the head priest, Meleake Tsion Kesis Addis Molaw and event organizers.

Class of 2023 5K Run/Walk Winners

Females: 15 – 30 years old Group
1st. Yeabsra Berhanu / የብስራ ብርሃኑ
2nd. Mena Feleke / መና ፈለቀ
3rd. Lia Lantyderu / ሊያ ላንተይደሩ

Males: 15 – 30 years old Group
1st. Bisrat Gebre / ብሰራት ገብሬ
2nd. Kaleab Assefa / ካሌብ አሰፋ
3rd. Nathan Yohannes / ኔተን ዮሐንስ
4th. Naom Ewinetu / ናኦም እውነቱ

Females: 30+ years old Group
1st. Yeshi Getahun / የሺ ጌታሁን
2nd. Yeshiwork Zenebe / የሺወርቅ ዘነበ
3rd. Tigist Mengistu / ትእግስት መንግስቱ
4th. Genet Gebremichael / ገነት ገብረሚካኤል

Males: 30+ years old Group
1st. Kinfe Ashu / ክንፈ ኣሹ
2nd. Mitiku Desalegn / ምትኩ ደሳለኝ
3rd. Ephrem Ghida / ኤፍሬም ጊዳ
4th. Tewodros Desta / ቴዎድሮስ ደስታ
5th. Estefanos / እስጢፋኖስ
6th. Dawit Worku / ዳዊት ወርቁ
7th. Ashebir / አሸብር

ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት በመርኃ ግብሩ ተካፊይ ለሆኑ እና ለመርኃ ግብሩ አዘጋጆች በሙሉ ቤተ ክርስቲያን ምሰጋናዋን ታቀርባለች::

Thank you to the church members, families and event organizers who made the 9th 5K run and walk a success!.

SCHEDULE YOUR TENT, TABLE AND CHAIR RENTAL IN OUR CHURCH! ወንበር፣ ጠረጴዛ እና ድንኳን መከራየት ይፈልጋሉ?

ለተለያዩ ዝግጅቶች ወንበር፣ ጠረጴዛ እና ድንኳን፣ በተመጣጣኝ ዋጋ መከራየት ሲፈልጉ ዶ/ር ብርሃኑ በለጠን በስልክ ቁጥር 612-644-2598 ይደውሉ ወይም ቴክስት ያድርጉ::

Do you know that our church offers rental services for tents, tables, and folding chairs for any event or party at very reasonable prices? Please call or text Dr. Berhanu Belete at 612-644-2598.

Church Members Meeting is Scheduled for July 2, 2023 / የቤተ ክርስቲያን አባላት ስብሰባ በመጪዉ እሁድ ሰኔ 25 2015

በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአባላት ስብሰባ በመጪዉ እሁድ ሰኔ 25 2015 (July 2nd, 2023) ይደረጋል:: ስብሰባው የቅዳሴ አገልግሎት እንደተጠናቀቀ ስለሚጀመር ፤ እባክዎ የስብሰባዉ ተካፊይ እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota will hold all church members meeting on July 2, 2023 after Sunday church services. Please attend.

Nineth Annual 5K Run and Walk Scheduled for July 1st, 2023 @ Phalen Park, St Paul, MN.

በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 9ኛውን የ5000 ሜትር ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በመጪዉ ቅዳሜ ሰኔ 24 2015 (July 1st, 2023) አዘጋጅቷል፤

Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota will hold its 9th annual 5K run and walk on July 1st, 2023 @ Phalen Park, St Paul, MN. Please mark your calendar.

Registration Fee: $25 / person

Race Venue/Address 
Phalen Park 
1600 Phalen Dr.
St. Paul MN 55106

Start Time: 7:30 AM
End Time:  12:00 PM

Race T-shirt Pickup at Phalen Park on the race day.

Registration Form – Age Groups 15 to 30 and above 30 years old.
Award: Male & Female by age groups.
      1st Place : Medal and Certificate
      2nd Place : Medal and Certificate
      3rd Place : Medal and Certificate

Contact for more information: Heyente Senay 612-554-2195

የሕማማት እና የትንሣኤ አገልግሎት በደብራችን

 

 

 

 

 

ከሰኞ – ረቡዕ  –> ከጠዋቱ 12 – ቀኑ 7 ሰዓት (6AM – 1 PM)
ሐሙስ  –>  ከጠዋቱ 11 – ቀኑ 8 ሰዓት (5AM – 2 PM)
አርብ  –>  ከጠዋቱ 11 – 12 ሰዓት (5AM – 6 PM)
ቅዳሜ  –> ጠዋት ከ12 – 2 ሰዓት
የትንሳኤ አገልግሎት
ቅዳሜ ከሰዓት 11  – ሌሊቱ 8 ሰዓት (ከ5PM – 2AM)

በዓለ ጥምቀት

ጥምቀት በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒያ በግእዝ አስተርዮ በአማርኛ መገለጥ ይባላል፡፡ ቃሉ በቀጥታ ሲተረጎም በውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት፣ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጥለቅ ማለት ነው፡፡ ጥምቀት ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን (ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ሜሮን፣ ምሥጢረ ቁርባን፣ ምሥጢረ ንስሐ፣ ምሥጢረ ክህነት፣ ምሥጢረ ተክሊል፣ ምሥጢረ ቀንዲል) አንዱና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ በዮሐ. 3፥5 ላይ ‹‹እውነት እውነት እልሀለሁ፤ ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡›› ብሎ እንደተናገረው ከውኃና ከመንፈስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት ኃጢአታችን የሚደመሰስበት ድኅነትን የምናገኝበት ዐቢይ ምሥጢር ነው፡፡ ጥምቀት በምሥጢረ ሥላሴና በምሥጢረ ሥጋዌ አምኖ ለሚፈጽመው ሰው ሁሉ ለኃጢአት መደምሰሻ ከሥላሴ የጸጋ ልጅነት ለመቀበልና የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ የተሰጠ ልዩ የሕይወት መንገድ ነው፡፡

to read more

Revised Bylaw (የተሻሻለው ህገ ደንብ)

Section 1 – Name The official name of the church shall be DEBRE SELAM MEDHANEALEM ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH in Minnesota, hereinafter referred to as “The Church”, which has been duly incorporated, AS A CONGREGATIONAL CHURCH, under Article 10, Section 191 and 193 of the Religious Incorporation Law of the State of Minnesota. English Version  የአማርኛ ቅጂ

English –  new Bylaw by SubCommittee

Orginal Posted on Aug 21, 2016 @ 07:57

የመድኃኔዓለም ንግስ እና የመሰረት ድንጋይ ማኖር በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁፅ አቡነ ዳንኤል በተገኙበት የጥቅምት መድኃኔዓለምን ጥቅምት 27 2009 (Nov 6, 2006) በደመቀ መልኩ ያከብራል በዕለቱም አዲስ በተገዛው ቦታ ላይ ብፁፅ አባታችን የመሰረት ድንጋይ ያኖራሉ።

ወስብሃት ለእግዚአብሔር!

ደብረ ሰላም 2.7 Acres (1.1 ሔክታር ወይንም 10927 ካሬ ሜትር) ቦታ ገዛች

2016-06-20 08_32_31-New notification በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።

“የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንሰራለን” ነህምያ 2፥20

ከሁሉ አስቀድሞ ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ለሰራ ለልዑል እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን።

ቤተክርስቲያናችን ሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚሰጡባት ንጽሕት እና ቅድስት የሆነች የእግዚአብሔር ማደሪያ ናት። ይህች ቤተክርስቲያን በፈቃደ እግዚአብሔር ከተመሰረተች ጊዜ ጀምሮ እዚህ ለምንገኝ አባላትም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች አሁን በዚህ ከእኛ ጋር ለሌሉም ብዙ ወገኖቻችን ሁሉ በርካታ አገልግሎቶችን ያበረከተች ቤተክርስቲያን ናት። ብዙዎች ልጆቻቸውን ያስጠመቁባት ቅዱስ ጋብቻን የመሰረቱባት ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ የበቁባት በርካቶችም ከጭንቀት ከሃዘንና ከችግራቸው የተጽናኑባት የሰማይ ደጅ ናት።

በእውነተኛው አምላካችን ደም የተመሰረተችው ይህች ቤተክርስቲያናችን የንጽህት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ቤተክርስቲያንን እምነት ሥርዓትና ትውፊት ጠብቃ ያለች በዓመት ውስጥ 365 ቀናት ክፍት ሆና በርካታ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ትሰጣለች። በኪዳን፣ በቅዳሴና በሰዓታት ጸሎታት፤ እንዲሁም በተለያዩ ክብረ በአላት፦ ለማስታወስም በአመት ውስጥ 14 ጊዜ ያህል በማኅሌት፣ ጥምቀትን ጨምሮ ዘጠኝ ጊዜ ያህል በንግሥ፣ 16 ቀን በሰሙነ ፍልሰታ፣ 6ሳምንታት በጽጌ ማኅሌት፣ 5 ቀን በሰሙነ ሕማማት እንዲሁም በመስቀል ደመራ ልዩ ዝግጅት ያላሰለሰ አገልግሎት የሚሰጠባት ታላቅ ደብር ናት።

በደብራችን የሚሰጡት መንፈሳዊ አገልግሎቶች እየተስፋፉ ከመምጣታቸው በተጨማሪ የተገልጋዩም ምእምን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ በመምጣቱ፤ ይበልጡንም ደግሞ በዚህ ሃገር የተወለዱ ልጆች ሃይማኖታቸውን ተምረው ቤተክርስቲያንን ለመረከብና ለማገልገል ይችሉ ዘንድ የተመቻቸ ሁኔታን ማዘጋጀት የግድ አስፈላጊ በመሆኑ በተጨማሪም ሌሎች ችግሮችን ማቃለል ይቻል ዘንድ በስፋትና በይዘት አሁን ካለንበት ቤተክርስቲያን ሰፋ ያለና ምቹ የሆነ ሁሉን የሚያሟላ አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን መስራት አማራጭ የሌለው መሆኑ ታምኖበት እንቅስቃሴ ተጀምሮ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጂ መልካም ሥራን ለመስራት ሲነሳሱ ሁል ጊዜም ፈተና በመኖሩ ያሰብነው እቅድ ቤተክርስቲያናችን በገጠማት ፈተና ለጊዜው ተጓቶ የነበረ ቢመስልም የቤተክርስቲያናችን የአስተዳደር ቦርድ ለዚህ ታላቅ ውጥን ቅድሚያ በመስጠት በተለያዩ ጊዜያትም ከአባላት ጋር በመወያየት እና የአባላትን ይሁኝታ በማግኘት ለጉዳዩ የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ሲሰራ ቆይቷል።

በእኛ በኩል ላለፈው አንድ አመት ተኩል ያህል ነገሮች አንድ ጊዜ ተስፋ የሚያስቆርጡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ተስፋ የሚሰጡ መስለው ሲቀጠሉ ቆይተዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር አምላክ ፈቅዶ ይኸው ለዛሬዋ የምስራች እለት አድርሶናል።

የምሰራቹም አንድ ዓመት ከአምስት ወራት ብዙ ውጣ ውረድ ያየንበት ለቤተክርስቲያን እና ለልዩ ልዩ ተቋማት መስሪያ የሚሆነውን 2.7 ኤከር ስፋት ወይንም ወደ 11 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለውን 2629 30th Ave S Minneapolis, 55406 ላይ የሚገኘውን ቦታ ገዝተን የቦታውን ባለቤትነት ሰነድ ከትናንት በስቲያ አርብ ጁን 17/2016 ዓ.ም ተረክበናል።

ለዚህም አባታችን መድኃኔዓለም ክብርና ምስጋና ለስሙ ይሁን እንላለን።

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤተ ክርስቲያን

 

በዓለ ስቅለት እና በዓለ እግዝእትነ ሲገጣጠሙ ይሰገዳል ወይስ አይሰገድም?

IMG_1421ምንም እንኳ ይህ ጥያቄ በብዙ ሰዎች ዘንድ የተመለሰ ቢሆንም ተደጋጋሚ ጥያቄዎች መምጣታቸው ሁለት ነገሮችን ስላመለከተኝ እኔም እንደገና በአጭሩ ለመመለስ ጥረት አደርጋለሁ፡፡ የመጀመሪያው የተሰጠው መልስ ለሁሉም እኩል አለመድረሱ ሲሆን በሁለተኛነት ደግሞ አንዳንዶቻችንም ተደጋሞ አንድ ዓይነት መልስ በማየት የማረጋገጥ ፍላጎት ያለን ይመስላል፡፡
ይህን የመሰሉ ተደጋጋሚ ጥቄዎች ሲገጥሙን ነገሩን ማየት ያለብን ከመሠረታዊው የቤተ ክርስቲያን ትውፊትና አስተምህሮ መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ ይህ ጥያቄ የበዓሉን አከባበር የሚመለከት ስለሆነ በቤተ ክርስቲያናችን የበዓላት ቀኖናም ሆነ ትውፊት መሠረት በዓላት የሚበላለጡ ከሆነ የሚበልጠው የትኛው ነው ከሚለው ቀላል ጥያቄ ልንነሣ እንችላለን፡፡ በዚሁ መሠረት የመጀመሪያውን ደረጃ የሚይዙት የጌታችን ዐበይት በዓላት ቀጥሎም የጌታችን ንዑሳት በዓላት መሆናቸውን ለመረዳት አያስቸግርም፡፡ Continue reading በዓለ ስቅለት እና በዓለ እግዝእትነ ሲገጣጠሙ ይሰገዳል ወይስ አይሰገድም?