Building Coordinating Committee By-law
እናስተዋውቃችሁ
የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የህንጻ ግንባታ ኮሚቴ
ኮሚቴው የቤተክርስቲያኑ አባላት በሆኑ ፈቃደኛ ግላሰቦች የተደራጀ ሲሆን 28 የሚሆኑ አባላትን አቅፏል።
ዓላማው: አዲሱን የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ህንጻ አሰርቶ ማስረከብ ነው።
ኮሚቴው ከተዋቀረበት ጉዜ አንስቶ ብዙ ነገሮችን የልዑል እግዚአብሄር ፈቃድ ታክሎበት አክናውሏል።
በመጀመሪያ የመተዳደረያ ደንብ አርቅቆ ተወያይቶበትና ተከራከሮበት ለቤተክርስቲያኑ የአስተዳደር ቦርድ አቅርቦ ካጸደቀ በኋላ በደንቡ መሠረት እራሱን አደራጀቶ ሥራዉን ጀምሯል።
መዋቅሩ: 7 አባላት ያሉት የሥራ አስፈፃሚ (Executive Committee) እና 4 ንዑሳን ኮሚቴዎችን የያዘ ነዉ። ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።