አባቶቻችን፡ ሊቃውንተ፡ ቤተክርስቲያን፡ እንደሚተርኩት፡ ማህበር፡ የሚለው፡ ቃል፡ ሲተረጎም፡ በአንድነት፡ በመተባበር፡ መኖር፡ ማለት፡ ሲሆን፡ ቃሉ፡ የግዕዝ፡ ቃል፡ መሆኑን፡ ይነግሩናል። በማያያዝም፡ በምድራዊው፡ ዓለም፡ በማህበር፡ ወይም፡ በመተባበር፡ መኖር፡ የተጀመረው፡ ከቀዳሚዎቹ፡ ፍጥረታት፡ ከአባታችን፡ ከአዳምና፡ ከእናታችን፡ ከሔዋን፡ ጊዜ፡ ጀምሮ፡ እንደሆነ፡ እና፡ ከዚያም፡ በኋላ፡ ልጆቻቸውና፡ የልጅ፡ ልጆቻቸው፡ አሁን፡ እኛ፡ እስካለንበት፡ ዘመን፡ ድረስ፡ በተለያየ፡ መልኩ፡ ሲጠቀሙበት፡ እንደቆዩ፡ እና፡አሁንም፡ እየተጠቀሙበት፡ መሆኑን፡ ለቃውንተ፡ ቤተክርስቲያን፡ በሰፊው፡ ያስረዳሉ። እንዲሁም፡ ማህበር፡ ከምድራዊ፡ ሰዎች፡ ብቻ፡ ሣይሆን፡ በሠማያዊያን፡ መላዕክት፡ ዘንድም፡ በዓለመ፡ መላዕክት፡ ማህበር፡ መኖሩን፡ ይህም፡ ማህበር፡ በዘጠና፡ ዘጠኝ፡ ነገደ፡ መላዕክትና፡ በዘጠና፡ ዘጠኝ፡ የነገድ፡ አለቆች፡ የተከፋፈለና፡ የተመደበ፡ መሆኑን፡ መምህራንና፡ መጻህፍት፡ ይነግሩናል።
የመድሐኔዓለም ጽዋ ማህበርን በሚመለከት ጥያቄ ካለዎት?
Eddel Senay / እድል:ሰናይ 763-350-9360