Category Archives: Uncategorized

እናስተዋዉቅዎት! የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. መርኃ ግብር

በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ መዝ.64፥11

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እግዚአብሔር አምላካችን በቸርነቱ ዓመታትን ለሁሉም ያቀዳጃል ከዓመት ወደ ዓመት በቸርነቱ ያሸጋግረናል። ያለፈው ዓመትን አሳልፎ አዲሱን ዓመት ስንቀበል ለሰራናቸው መልካም ስራዎች እውቅና ሰጥተን ጀምረን ያልጨረስናቸውን ደግሞ ለከርሞ ጨርሰን ልንሰራ ያሰብናቸውን ደግሞ እግዚአብሔርን አጋዥ አርገን እንሰራለን።

ከተመሰረተ 27 አመት ያስቆጠረዉ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያናችን ውስጥ ዓመት በዓመት ብዙ እንቅሳቃሴ እያደረገ እንዳለ የሚታወቅ ነዉ:: የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት በውስጡ ታዳጊ እና ወጣቶችን አቅፎ የሚንቀሳቀስ ለቤተክርስቲያናች ተጠሪ ተቋም ነው። ሰንበት ትምህርት ቤታችን 9 የአገልግሎቶች ክፍሎች አሉት:: ከነዚህም ዉስጥ የልጆች ትምህርት ክፍል አገልግሎት ዘርፈ ብዙ የሆኑ ልዩ ልዩ ትምህርታዊ እና ማህበራዊ አገልግሎቶች ይሰጡበታል:: የደብረሰላም መድኃኔአለም የልጆች ክፍል አገልግሎቶችን በዝርዝር የሚገልፅ ፅሑፍ ከዚህ ቀደም አቅረበናል:: ለማንበብ ይህንን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ::

የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት መርኃ ግብር እና እንቅስቃሴ ሃይማኖታዊ የበጎ አድራጎት እና ማህበራዊ አገልግሎቶችን ይጨምራል::

  1. በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. በኢትዮጵያ የሚገኘው ሜሪጆይ በሚባል የእርዳታ ድርጅት ስር ካሉ ልጆች መካከል የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት 20 ልጆችን ይረዳል::
  2. የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትን በማስተባበር በካሊፎርኒያ ለሚገኘው ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም የ $3000 ዶላር እርዳታ አበርክቷል።
  3. የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በማህሌት አገልግሎት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ::
  4. የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በዓመቱ መጀመሪያ ላይ በቤተክርስቲያናችን ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6 ለ6 ሳምንታት በሚደረገው ጽጌ ማህሌት ላይ በመገኘት አገልግሎቱ እንዲጠነክር ጉልህ አስተዋጾ ያደርጋሉ::
  5. የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በበዓለ ንግስ ላይ በዝማሬ ያገለግላሉ::
  6. የደብረ ታቦር በዓልን የኢትዮጵያን ቱፊት ሳይለቅ፣ ሃይማኖታዊ ይዘቱን እንደያዘ፣ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሆያ ሆዬ በመዘመር እና የችቦ ማብራት መርኃ ግብር በማዘጋጀትና በመምራት የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
  7. አዲስ ዓመትን የኢትዮጵያን ቱፊት ለቅ፣ ሃይማኖታዊ ይዘቱን እንደያዘ፣ እንኳን አደረሳችሁ በማለት እና አበባይሆሽ በመዘመር ወግና ስርአቱን ለትውልድ ለማስተላለፍ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
  8. በተለያዩ ጊዜያት ከሌሎች የደብራችን አባላትና ቤተሰቦች ጋር በመሆን በዩኤስ ባንክ ስታዲየም ለአዲስ ቤተክርስቲያን ማሰሪያ የሚውል የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ላይ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት አስተዋጽኦ ሲያደርጉ ቆይቷል።

የ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ልዩ ልዩ ተጨማሪ ክንዋኔዎችን በሚመለከት:-

ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ተማሪዎች በማህሌት አገልግሎት ላይ ነዉ::

ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ተማሪዎች በኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስ ላይ በዝማሬ ሲያገለግሉ ነዉ::

ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ተማሪዎች በበገና ምሽት መርኃ ግብር ላይ በበገና ዝማሬ ሲያቀርቡ ነዉ::

በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ከተዘጋጁት እና ስኬታማ ከሚባሉት መርኃ ግብር መካከል አንዱ የቤዛ ኩሉ ስንበት ትምህርት ቤታችን የ27ተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ነበር። ክብረ በዓሉ በተጋባዥ መምህራን ቃለ እግዚአብሔር የተሰጠበት ደማቅ እና የማይረሳ ነበር። በዚህ መርኃግብር ላይ የቤዛ ኩሉ ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ሆነው 2ተኛ ክፍልን ላጠናቀቁ ልጆች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት ነሐሴ 13 የደብረ ታቦርን በዓል በማስመልከት ፈቃደኛ በሆኑ ምእመናን መኖሪያ ቤቶች ድረስ በመሄድ ሆያ ሆዬ በመዘመር ለአዲስ ቤተክርስቲያን ሕንጻ ማሰሪያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ላይ ነዉ።

የደብረ ታቦር በዓልን የኢትዮጵያን ቱፊት ሳይለቅ፣ ሃይማኖታዊ ይዘቱን እንደያዘ፣ ለትውልድ ለማስተላለፍ ሆያ ሆዬ በመዘመር እና የችቦ ማብራት መርኃ ግብር በማዘጋጀትና በመምራት የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል:: ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት ተማሪዎች የደብረ ታቦር (ቡሔ) የችቦ ማብራት መርኃ ግብር ላይ ሲዘምሩ ነዉ ::

የቤዛ ኵሉ ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች አዲስ ዓመትን እንኳን አደረሳችሁ በማለት የኢትዮጵያን ቱፊት ስይለቅ፣ ሃይማኖታዊ ይዘቱን እንደያዘ ለትውልድ ለማስተላለፍ የበኩሉን አስተዋጾ እያደረገ ይገኛል። በመሆኑም ከዚህ በታች ያለዉ የሚያሳየዉ የቤዛ ኵሉ ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች ፈቃደኛ በሆኑ ምእመናን መኖሪያ ቤቶች ድረስ በመሄድ አበባይሆሽ በመዘመር ለአዲስ ቤተክርስቲያን ሕንጻ ማሰሪያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ተከናውኗል።

አዲሱ ዘመን የደስታ የሰላም የፍቅር የይቅርታ የንስሀ ይሁንልን
የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ዘወትር እሁድ ከቅዳሴ በኋላ 11፡30 AM ጀምሮ እስከ 1 PM ተከታታይ ትምህርት እንዲሁም በአባታችን በሊቀ ጠበብት መራዊ እና በወንድማችን አጋፋሪ ብርሃኑ ያሬዳዊ ዜማ እና ልዩ ልዩ መርኃግብሮች ይሰጣሉ:: መጥተው አብረን በአገልግሎት እንጠንክር።

እንድናገለግለው የፈቀደልን እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን
የእመቤታችን የድንግል ማርያም ምልጃ አይለየን

ይህን ጽሁፍ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ያዘጋጀችው እህታችን ወይዘሮ ሐና ስዩም ነች:: እባካችሁ አመሰግኑልኝ!

ለተጨማሪ ማብራሪያ?
• አቶ ዮሐንስ ከበደ 612-707-5212
• ወ/ት ማርታ 952-437-4312
• ወ/ት ማህሌት ተፈራ 651-442-3738
• አቶ ይገርማል ፈጠነ 651-332-6098
• አቶ እርስት መኮንን 952-221-6668
• አቶ ደባልቄ ገበየሁ 612-203-7745

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ኢሜይል: membersservice@dsmachurch.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
Facebook: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ!

በሥመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱሥ አሀዱ አምላክ አሜን!!!

በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። መዝ ፷፬፥፲፩

የተከበራችሁ የቤተክርስትያችንና አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤
እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ እያልን መጭው ዓመት የሰላም ፣ የጤና እንዲሁም የፍቅር ዓመት እንዲሆንላችሁ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ እየተመኘን እንደወትሮዉ ሁሉ በዚህ ባጠናቀቅነዉ የ፪ሺ፲፭ ዓ.ም የሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዓመቱን በሙሉ ክፍት ሆና ዘወትር በየአዘቦት ቀናቶች የኪዳን አገልግሎት፣ ዘወትር እሁድ የኪዳን ፀሎት፣ ቅዳሴ እና ማህሌት፣ እንዲሁም የንግሥ በአላት ፀሎት እና የቅዳሴ አገልግሎቶች፣ የክርስትና፣ ቅዱስ ጋብቻ፣ ፀሎተ ፍታት አገልግሎቶችን ሰጥታለች::

እንደሚታወቀው ሁሉ ደብራችን የሚንቀሳቀስው ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በበጎፈቃደኞች ግልጋሎት እና እገዛ ነው:: እንደወትሮው ሁሉ በዚህ አመትም ብዙ የደብራችን አባላት በተለያዩ የስራ ዘርፎች በፈቃደኝነት በመሳተፍ ውድ ጊዜአቸውን ጉልበታቸውን እውቀታቸውን እና ገንዘባቸውን በተለያዮ ጊዜእት ለቤተክርስቲያናችን አበርክተዋል:: ለመጥቀስም ያህል በቤተክርስታያን ጽዳት ምግብ ሻይና ቡና በማቅረብና በማዘጋጀት በአባላት ማህበራት ውስጥ በአመራርነት በመሳተፍ ህጻናትን እና ወጣቶችን በመንፈሳዊ እውቀት እና በግብረገብነት በማነጽና በመምራት ህንጻ ኮሚቴ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ላይ በበጎፈቃድ የስራ ቦታዎች በመሳተፍ በመንፈሳዊ አገልግሎቱም በኩል በበጎፈቃደኝነት በመሳተፍና በሌሎችም እዚህ ባልተጠቀሱ ግልጋሎቶች ሁሉ በመሳተፍ:: በዚህ አጋጣሚ የአስተዳደር ቦርዱ ለደብራችን በጎፈቃደኞች ሁሉ የከበረ ምስጋናውን ያቀርባል:: መድሀኔአለም በበረከቱ ይጎብኛችሁ::

በተጨማሪም በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ዘርፈ ብዙ የሆኑ ልዩ ልዩ ማህበራዊ እና ትምህርታዊ አገልግሎቶች ተሰጥተዋል:: ለመጥቀሰም ያህል:-
1. ወጣቶች ስርዓተ ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ በሊቃውንት አባቶች የድቁና ትምህርት ተሰጧቸው ድቁንና ተቀብለዋል::
2. በበጎፈቃደኞች
እርዳታ ለልጆችና ወጣቶች መንፈሳዊ የበገና ትምህርት ተሰጧቸዋል።
3. በበጎፈቃደኞች እና በወላጆች እርዳታ ልጆችና ወጣቶች መንፈሳዊ እና የአማርኛ ቋንቋ ትምህርትን ይከታተሉባታል::

የ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ልዩ ልዩ ተጨማሪ ክንዋኔወችን በሚመለከት:-
4.
ደብራችን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የአስተዳደር ቦርድ አባላት ምርጫ ለ12ኛ ጊዜ ተካሂዶ አዲስ የተመረጡት የአስተዳደር ቦርድ አባላት የሶሰት አመት የስራ ዘመናቸውን ቃለ መሀላ በመፈፀም ጀምረዋል::
5. በዚህ በጨረስነው አመት 68 ቤተስቦች ደብራችንን በአዲስ አባልነት ተቀላቅለዋል:: እንኳን ደህና መጣችሁ እንላቸዋለን::
6. ቤተክርስቲያናችን
12 ክፍል እና ከኮሌጅ ትምህርታቸዉን ላጠናቀቁ 12 የቤተክርስቲያናችን ወጣቶች የእንኳን ደስ ያላችሁ የምስክር ወረቀት አበርክታለች::
7. አዲሱን የቤተክርስቲያናችንን ሕንፃ ለመገንባት የሚያስፈልገንን ገንዘብ ለማሰባሰብ ከኪሳችን ከምናዋጣው ገንዘብ በተጨማሪ ነፃ የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ ማሰባስቡን ስራ እንደወትሮዉ ሁሉ በዩኤስ ባንክ ስታዲየም ቀጥለንበት እንገኛለን:: በዚሁ በተጠናቀቀው የ፪ሺ፲፭ ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ ስቴት ፌር የስራ መስክ ተቀይሶ በበጎፈቃደኝነት
አገልግሎት የገንዘብ ማሰባስቡ ስራ በጥሩ ውጤት ተጠናቋል::

8. አባላት እና ቤተሰቦቻቸው በፌለን መናፈሻ ውስጥ ለዘጠነኛ ጊዜ የተዘጋጀውን የ5,000 ሜትር ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በደመቀ መልኩ ተሳትፈው መርኃ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል:: በእለቱም አሸናፊዎች የተዘጋጀላቸውን ሜዳልያና ምስክር ወረቀት ከደብራችን አስተዳዳሪ ከመልአከ ጽዮን ቀሲስ አዲስ ሞላው እና ከመርኃ ግብሩ አዘጋጆች ተቀብለዋል::

9. በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. የቤዛ ኩሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የ27ኛ ዓመት ምስረታ በዓል በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ በድምቀት ተከብሯል።

10. በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ለህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶች ለአንድ ሳምንት የቆዬ የሰመር ካምፕ ዝግጅቶች በጥሩ ውጤት እና በሰላም ተጠናቋል:: የሰመር ካምፑ የተለያዩ ልጆችን የሚስተምሩ እና የሚያዝናኑ ዝግጅቶች ነበሩት::

11. በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ለሁለት ሳምንት የቆዬ የልጆች ሰመር ኮርስ (summer courses) በሰላም ተጠናቋል::

12. በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ከዶ/ር ሲራክ በተገኘ የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ እርዳታ ህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶችን ያሳተፈ በበንከር የውሀ ዳርቻ (Bunker beach) እና Valley Fair የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ (field Trip) በደመቀ መልኩ ተጠናቋል::

አዲሱ ዘመንም የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን:: በ፪ሺ፲፮ዓ.ም ቃለ እግዚአብሔር ለመማር፣ ንስሐ ለመግባት፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ያብቃን።

ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት ብለን የምናመሰግነው፣ ዘመናትን የሚያስረጃቸው፣ ዘመናትን የፈጠረ እና ሰፍሮ ለሰው ልጅ የሰጠ ልዑል እግዚአብሔር መጨው ፪ሺ፲፮ ዓመተ ምህረትን ባርኮ ለቤተክርስቲያን ይስጥልን፤ የመከራውን ዘመንም በቃ ይበለን፤ የእመአምላክ እናትነቷ ምልጃና ርህራሄ አይለየን ፤ አስራት ሀገሯን ኢትዮጵያም በቀደመ ክብሯ ታስብልን አሜን!!!

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ
መስከረም ፩ ፪ሺ፲፮ ዓ.ም
ሚኒአፖልስ ሚኒሶታ
September 12, 2023, Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

ለተጨማሪ ማብራሪያ ጥያቄ ካለዎት?
እርስት መኮንን 952-221-6668
ደባልቄ ገበየሁ 612-203-7745

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
Website: https://www.debreselam.net
Facebook: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

በኦገስት እስከ 14 የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች አሉ / 14 volunteer days in August. Let’s go DSMA!

ዲሱን የቤተክርስቲያናችንን ሕንፃ ለመገንባት የሚያስፈልገንን ገንዘብ ለማሰባሰብ ከኪሳችን ከምናዋጣው በተጨማሪ ነፃ የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በስታድየም እየሰጠን እንገኛለን:: የእናንተን ቀና ትብብር በመተማመንና ተስፋ በማድረግ በዩኤስ ባንክ ስታድየም በተጨማሪ ሌላ አማራጭዎችን በመፈለግ ላይ እንገኛለን::

በዚህም ፍለጋ ሂደት በመጭው የሚኔሶታ ስቴት ፌር (MINNESOTA STATE FAIR) ከ THURSDAY, AUGUST 24, 2023 – MONDAY, SEPTEMBER 4, 2023 ለ12 ቀናት በመስራት ገንዘብ ለመሰሰብ አጋጣሚው አለን::
ስራው:- ፓርኪንግ ጥበቃ
ሰዓት :- 6 ኤኤም እስከ 8 ፒኤም
የሰው ቁጥር:- 5 ወይም 7 በአንድ ፓርኪንግ ሜዳ
የፓርኪንግ ሜዳዎች ቁጥር:- 5

እባክዎን ሚኔሶታ ስቴት ፌር የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት July 23, 2023 ይመዝገቡ!

Thank you Dr Ashagre for diversifying our volunteer for church funds opportunity to include work at state fair events. There are 14 volunteer dates in August. Three days at US Bank Stadium (Aug 12, Aug 19 and Aug 26) and 12 days at MN State Fair (Aug 24 – Sept 4). As you would surmise Identifying and Coordinating the volunteer pool for the state fair events is the most pressing at the moment as we would need to know the number of volunteers by EOD Sunday July 23.

We are kindly asking all of you to consider registering as an individual or as a group for the state fair events from Aug 24 to Sept 4. There will be 7 weekdays and 5 weekends and public holidays during the event. The math is clear. The more days and/or the more parking lots we staff the more funds we will generate for our church. Let’s go DSMA!

ስለሆነም በኦገስት እስከ 14 የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት ቀኖች አሉ: እነሱም

  1. Saturday, Aug 12, 2023, Ed Sheeran Concert
  2. Saturday, 19 Aug 2023 | Tennessee Titans at Minnesota Vikings . Game starts at 7:00 pm | volunteer check in at 3 pm.
  3. Thursday, 24 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  4. Friday, 25 Aug 2023 | State Fair Parking Lots
  5. Saturday, 26 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  6. Saturday, 26 Aug 2023 | Arizona Cardinals at Minnesota Vikings | Game start at noon | volunteer check in at 8 am
  7. Sunday, 27 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  8. Monday, 28 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  9. Tuesday, 29 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  10. Wednesday, 30 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  11. Thursday, 31 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  12. Friday, 01 Sept 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  13. Saturday, 02 Sep 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  14. Monday, 03 Aug 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots
  15. Tuesday, 04 Sept 2023 | 6am – 8 pm | State Fair Parking Lots

SCHEDULE YOUR TENT, TABLE AND CHAIR RENTAL IN OUR CHURCH! ወንበር፣ ጠረጴዛ እና ድንኳን መከራየት ይፈልጋሉ?

ለተለያዩ ዝግጅቶች ወንበር፣ ጠረጴዛ እና ድንኳን፣ በተመጣጣኝ ዋጋ መከራየት ሲፈልጉ ዶ/ር ብርሃኑ በለጠን በስልክ ቁጥር 612-644-2598 ይደውሉ ወይም ቴክስት ያድርጉ::

Do you know that our church offers rental services for tents, tables, and folding chairs for any event or party at very reasonable prices? Please call or text Dr. Berhanu Belete at 612-644-2598.

Free Income Tax Preparation Service Initiative

Volunteers Needed

Learn to Prepare Taxes and Make a Difference at the same time.  How can you make a difference? Simple.  Help your community in preparing taxes free of charge or for a voluntary contribution to building funds by becoming a volunteer with the Free Income Tax Preparation Service Initiative.

Be a Volunteer.  This Free Income Tax Preparation Initiative is a partnership between Amare Berhie and Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, Minneapolis, Minnesota

Volunteers typically start training in January. They are expected to provide two to three hours (Sunday) of service per week between the beginning of February to the middle of April. The time commitment will vary depending on individual responsibilities as well as the number of volunteers working at a site and the number of people being served by the site.

Currently we are seeking volunteers for the following positions:

  • Administrative assistants to process tax returns, make copies, keep track of data, check taxpayers in, and make sure taxpayers are being served in the order they arrived
  • Interpreters assist taxpayers who have limited English proficiency. We are currently seeking Tigrigna and Oromia interpreters.

Volunteer Requirements:

  • Sign a confidentiality agreement;
  • Seniors in high school or university students planning to major in accounting, finance, marketing, business, etc.
  • Excellent typing speed.

Why Volunteer?

  • Learn something new and exciting.
  • Make an impact on the lives of others.
  • Improve language skills.
  • Meet and interact with new and diverse people
  • Give back to your community.
  • Gain valuable work and business experience to better compete in today’s job market.
  • Utilize your professional/technical skills.

Great volunteers are the key to our success. Join this year’s effort and help make a difference in our community.

Want More Information?

Call Ato Tewodros Desta @ 651-235-5341

Free Income Tax Preparation Service Initiative! (ነጻ የገቢ ታክስ ዝግጅት አገልግሎት)

Get Your Tax Refund Fast!!!

Combining e-file with direct deposit is the fastest and safest way to get your refund. Amare Berhie, an IRS licensed Enrolled Agent and an Authorized e-file Provider, is providing free tax preparation services in hopes of raising funds for Debre Selam Medhanealem EOTC building. You are welcome to make donations of any amount. Please come and take advantage of this offer to have your taxes completed by an experienced professional and your volunteered contribution will go to a good cause.(ከገቢ ታክስ ተመላሽ ክፍያ በተፋጠነ መንገድ ለማግኘት ሰነዱን በአሌክትሮኒክስ ገቢ በማድረግና ተመላሹ ገንዘብ ለባንክ በቀጥታ ገቢ እንዲሆን የሚያስችል የታክስ ዝግጅት አገልግሎት ባሁኑ ወቅት በቤተክርስትያናችን ይሰጣል።

 ለቤተክርስትያን ህንጻ ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ እንዲረዳ በማቀድ ለዚሁ ሙያ ህጋዊ ፈቃድና የምስክር ወረቀት ያላቸው ባለሙያ አቶ አማረ በርሄ ለግል ድካማቸው ክፍያ ሳይጠይቁ አገልግሎቱን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል። ለዚህም በጎ ተግባር አቅማችሁ የቻለውን ያህል በመለገስ ሰፊ የሥራ ልምድ ባለው ባለሙያ በአገልግሎቱ እንድትጠቀሙ ቤተክርስትያናችን ትጋብዛለች።)

Open Every Sunday 8:30am – 11:30am until April 15, 20174401 Minnehaha Avenue, Minneapolis, MN 55406To make appointment (651) 235-5341, (612) 424-1540

For more info visit https://www.debreselam.net or https://www.facebook.com/Debreselameotc

ደመራ 2010 (Demera 2017)

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ2010 ዓ. ም. (2017) የደመራ በዓልን በደመቀ ሁኔታ መስከረም ፲፫, ፳፻፲ (September 23, 2017) በ2629 30th Ave South Minneapolis MN 55406 ስለሚያከብር ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተካፊይ እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

በእለቱም ለልጆችዎ መጫወቻ ያዘጋጀን ስለሆነ ከ12PM ጀምሮ መጥተው ልጆችዎን ያጫውቱ።

የመኪና ማቆሚያ የተንጣለለ የ2.7 Acre ቦታ ስላለን ማቆሚያ ቦታ አጥቼ እቸገራለሁ ብለው ኃሳብ እይግባዎት፣ እንደ በፊቱ ሩቅ አቁሞ የጐልፍ ሜዳ አቋረጡ ብሎ የሚወቅስዎ የለምና ዘና ብለው መኪናዎትን ያቆሙ ዘንድ የሚረዱዎት መዕመናን አዘጋጅተን እንጠብቆታለን።

ወስበሃት ለእግዚአብሔር

Easter Live Broadcasting/የትንሣኤ አገልግሎት ቀጥታ ስርጭት

Easter Live Broadcasting – Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Church Minneapolis MN
የትንሣኤ አገልግሎት ቀጥታ ስርጭት – ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን – ሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ
Happy Easter – This will conclude our  live broadcast.
መልካም የትንሣኤ በዓል

የስቅለት አገልግሎት ቀጥታ ስርጭት

Good Friday Live Broadcasting – Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Church Minneapolis MN
የስቅለት አገልግሎት ቀጥታ ስርጭት – ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን – ሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ
Good Friday Live Broadcasting – 2
Good Friday Live Broadcasting –  1

የሕማማት እና የትንሣኤ አገልግሎት በደብራችን

 

 

 

 

 

ከሰኞ – ረቡዕ  –> ከጠዋቱ 12 – ቀኑ 7 ሰዓት (6AM – 1 PM)
ሐሙስ  –>  ከጠዋቱ 11 – ቀኑ 8 ሰዓት (5AM – 2 PM)
አርብ  –>  ከጠዋቱ 11 – 12 ሰዓት (5AM – 6 PM)
ቅዳሜ  –> ጠዋት ከ12 – 2 ሰዓት
የትንሳኤ አገልግሎት
ቅዳሜ ከሰዓት 11  – ሌሊቱ 8 ሰዓት (ከ5PM – 2AM)

በዓለ ጥምቀት

ጥምቀት በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋኒያ በግእዝ አስተርዮ በአማርኛ መገለጥ ይባላል፡፡ ቃሉ በቀጥታ ሲተረጎም በውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት፣ መነከር፣ መዘፈቅ፣ መጥለቅ ማለት ነው፡፡ ጥምቀት ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን (ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ሜሮን፣ ምሥጢረ ቁርባን፣ ምሥጢረ ንስሐ፣ ምሥጢረ ክህነት፣ ምሥጢረ ተክሊል፣ ምሥጢረ ቀንዲል) አንዱና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ በዮሐ. 3፥5 ላይ ‹‹እውነት እውነት እልሀለሁ፤ ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡›› ብሎ እንደተናገረው ከውኃና ከመንፈስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት ኃጢአታችን የሚደመሰስበት ድኅነትን የምናገኝበት ዐቢይ ምሥጢር ነው፡፡ ጥምቀት በምሥጢረ ሥላሴና በምሥጢረ ሥጋዌ አምኖ ለሚፈጽመው ሰው ሁሉ ለኃጢአት መደምሰሻ ከሥላሴ የጸጋ ልጅነት ለመቀበልና የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ የተሰጠ ልዩ የሕይወት መንገድ ነው፡፡

to read more

Revised Bylaw (የተሻሻለው ህገ ደንብ)

Section 1 – Name The official name of the church shall be DEBRE SELAM MEDHANEALEM ETHIOPIAN ORTHODOX TEWAHEDO CHURCH in Minnesota, hereinafter referred to as “The Church”, which has been duly incorporated, AS A CONGREGATIONAL CHURCH, under Article 10, Section 191 and 193 of the Religious Incorporation Law of the State of Minnesota. English Version  የአማርኛ ቅጂ

English –  new Bylaw by SubCommittee

Orginal Posted on Aug 21, 2016 @ 07:57

የመድኃኔዓለም ንግስ እና የመሰረት ድንጋይ ማኖር በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁፅ አቡነ ዳንኤል በተገኙበት የጥቅምት መድኃኔዓለምን ጥቅምት 27 2009 (Nov 6, 2006) በደመቀ መልኩ ያከብራል በዕለቱም አዲስ በተገዛው ቦታ ላይ ብፁፅ አባታችን የመሰረት ድንጋይ ያኖራሉ።

ወስብሃት ለእግዚአብሔር!

ደብረ ሰላም 2.7 Acres (1.1 ሔክታር ወይንም 10927 ካሬ ሜትር) ቦታ ገዛች

2016-06-20 08_32_31-New notification በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።

“የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንሰራለን” ነህምያ 2፥20

ከሁሉ አስቀድሞ ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ለሰራ ለልዑል እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን።

ቤተክርስቲያናችን ሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚሰጡባት ንጽሕት እና ቅድስት የሆነች የእግዚአብሔር ማደሪያ ናት። ይህች ቤተክርስቲያን በፈቃደ እግዚአብሔር ከተመሰረተች ጊዜ ጀምሮ እዚህ ለምንገኝ አባላትም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች አሁን በዚህ ከእኛ ጋር ለሌሉም ብዙ ወገኖቻችን ሁሉ በርካታ አገልግሎቶችን ያበረከተች ቤተክርስቲያን ናት። ብዙዎች ልጆቻቸውን ያስጠመቁባት ቅዱስ ጋብቻን የመሰረቱባት ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ የበቁባት በርካቶችም ከጭንቀት ከሃዘንና ከችግራቸው የተጽናኑባት የሰማይ ደጅ ናት።

በእውነተኛው አምላካችን ደም የተመሰረተችው ይህች ቤተክርስቲያናችን የንጽህት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ቤተክርስቲያንን እምነት ሥርዓትና ትውፊት ጠብቃ ያለች በዓመት ውስጥ 365 ቀናት ክፍት ሆና በርካታ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ትሰጣለች። በኪዳን፣ በቅዳሴና በሰዓታት ጸሎታት፤ እንዲሁም በተለያዩ ክብረ በአላት፦ ለማስታወስም በአመት ውስጥ 14 ጊዜ ያህል በማኅሌት፣ ጥምቀትን ጨምሮ ዘጠኝ ጊዜ ያህል በንግሥ፣ 16 ቀን በሰሙነ ፍልሰታ፣ 6ሳምንታት በጽጌ ማኅሌት፣ 5 ቀን በሰሙነ ሕማማት እንዲሁም በመስቀል ደመራ ልዩ ዝግጅት ያላሰለሰ አገልግሎት የሚሰጠባት ታላቅ ደብር ናት።

በደብራችን የሚሰጡት መንፈሳዊ አገልግሎቶች እየተስፋፉ ከመምጣታቸው በተጨማሪ የተገልጋዩም ምእምን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ በመምጣቱ፤ ይበልጡንም ደግሞ በዚህ ሃገር የተወለዱ ልጆች ሃይማኖታቸውን ተምረው ቤተክርስቲያንን ለመረከብና ለማገልገል ይችሉ ዘንድ የተመቻቸ ሁኔታን ማዘጋጀት የግድ አስፈላጊ በመሆኑ በተጨማሪም ሌሎች ችግሮችን ማቃለል ይቻል ዘንድ በስፋትና በይዘት አሁን ካለንበት ቤተክርስቲያን ሰፋ ያለና ምቹ የሆነ ሁሉን የሚያሟላ አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን መስራት አማራጭ የሌለው መሆኑ ታምኖበት እንቅስቃሴ ተጀምሮ የነበረ መሆኑ የሚታወስ ነው። ይሁን እንጂ መልካም ሥራን ለመስራት ሲነሳሱ ሁል ጊዜም ፈተና በመኖሩ ያሰብነው እቅድ ቤተክርስቲያናችን በገጠማት ፈተና ለጊዜው ተጓቶ የነበረ ቢመስልም የቤተክርስቲያናችን የአስተዳደር ቦርድ ለዚህ ታላቅ ውጥን ቅድሚያ በመስጠት በተለያዩ ጊዜያትም ከአባላት ጋር በመወያየት እና የአባላትን ይሁኝታ በማግኘት ለጉዳዩ የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ ሲሰራ ቆይቷል።

በእኛ በኩል ላለፈው አንድ አመት ተኩል ያህል ነገሮች አንድ ጊዜ ተስፋ የሚያስቆርጡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ተስፋ የሚሰጡ መስለው ሲቀጠሉ ቆይተዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር አምላክ ፈቅዶ ይኸው ለዛሬዋ የምስራች እለት አድርሶናል።

የምሰራቹም አንድ ዓመት ከአምስት ወራት ብዙ ውጣ ውረድ ያየንበት ለቤተክርስቲያን እና ለልዩ ልዩ ተቋማት መስሪያ የሚሆነውን 2.7 ኤከር ስፋት ወይንም ወደ 11 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለውን 2629 30th Ave S Minneapolis, 55406 ላይ የሚገኘውን ቦታ ገዝተን የቦታውን ባለቤትነት ሰነድ ከትናንት በስቲያ አርብ ጁን 17/2016 ዓ.ም ተረክበናል።

ለዚህም አባታችን መድኃኔዓለም ክብርና ምስጋና ለስሙ ይሁን እንላለን።

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤተ ክርስቲያን

 

Revised Bylaw (የተሻሻለው ህገ ደንብ)

As you / members of our Church / are aware that the board of trustees of Minnesota Debreselam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church had assigned a committee to review the bylaw of our Church and recommend amendments back to the board.

After the assigned committee had completed its task and submitted its proposals, the board of trustees on its part reviewed and approved the amendments having made some changes to some of the proposed amendments.

Since the final draft of the bylaw should be discussed and approved by members of the Church in a duly called General Assembly meeting, here posted are the proposed amendments to view and discuss.
The board of trustees will soon announce the date of the General Assembly meeting for discussion over these amendments and for approval by the GA.

RevisedBylaw

Amharicbylaw