Category Archives: Holdays

የኅዳር ሚካኤልን በዓለ ንግስ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ!

የኅዳር ሚካኤል በዓለ ንግስ እሁድ ህዳር 9, 2016 በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ ይከበራል:: መጥተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች::

መቼ? / When?
እሁድ ህዳር 9, 2016 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ
Sunday Nov. 19, 2023 from 2:00 am

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406 ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
Website: https://www.debreselam.net

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ / Click Here to Follow Us On Facebook

የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስን በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

የዘንድሮዉ የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስ በደመቀ ሁኔታ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይከበራል:: መጥተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

መቼ? / When?
ማነክሰኞ ነሐሴ 16, 2015 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ
Tuesday August 22, 2023 from 2:00 pm

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ / Click Here to Follow Us On Facebook

የደብረ ታቦር ክብረ በዓልን በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

መቼ? / When?
ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ
Saturday August 19, 2023 from 4:00 pm

የዚህ ዓመት የደብረ ታቦር ክብረ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 (Saturday August 19, 2023) ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ዝግጅትይከበራል። እርስዎም መጥተው የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ የቤዛ ኩሉ የሰንበት ትምህርት ቤት ጥሪውን ያቀርባል።

ደብረ ታቦር (Transfiguration- Debre Tabor)

የሚካኤል በዓለ ንግስና የምስጋና ቀን June 20 & 21, 2015

St_MichaelJune 20
ከ3 – 5PM የቅዱስ ሚካኤል ዋዜማ
ከ5 – 9PM የምስጋና ዝግጅት (ቸሩ አባታችን በMay 11, 2014 በቤቱ ስላቆየን)

June 21
ከ3AM – 7AM ማኅሌት
ከ7AM – 10AM ስርዓተ ቅዳሴ
ከ10 AM – 12PM  መዝሙር፣ ስብከተ ወንጌል፣ ስርዓተ ንግስ
መጥተሁ ከቅዱስ ሚካኤል በረከት ይካፈሉ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

ዳግመ ትንሳኤ

PalmSunday30የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤተ ክርስቲያን ከሆሳዕናና ከመድኃኔዓለም ንግስ ጀምሮ ፣ በሰመነ ህማማት፣ በጸሎተ ሐሙስ፣ በስቅለትና ከትንሳኤው ዋዜማ ጀምሮ በጣም ብዙ ህዝብ በተገኘበት በዓላቱን በደመቀ መልኩ አክብሯል፤ እነሆ አሁንም ዳግመ ትንሳኤን ዘንድሮ ለመጀመሪያ ግዜ ከጠዋቱ 4AM ጀምሮ በማህሌት፣ በቅዳሴና በስብከተ ወንጌል ሊያከብር ስላሰበ እርሶም መጥተው የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Easter 2015 Video (የትንሳኤ አገልግሎት ቪዲዮ)

5ኛው ሳምንት፦ ደብረ ዘይት

ይህ ዕለት ደብረ ዘይት ይባላል። ስያሜው እንደቀደሙት ሰንበታት ሁሉ የቅዱስ ያሬድ ስያሜ ሲሆን በዚህ ቀን መድኃኒታችን ሁለተኛ በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት (በመለኮታዊ ግርማው በሰው መጠን) እንደሚመጣ የዓለምም ፍጻሜው እንዴት እንደሚሆን ለሐዋርያት በደብረ ዘይት ማስተማሩን እንዲሁም በክብር ያረገው ጌታን ለሚጠባበቁት ዋጋቸውን ላልተቀበሉትም ፍዳቸውን ሊከፍል የምድርን ሥርዓት ሊሽር ሰማይና ምድርን አሳልፎ ለወዳጆቹ መንግስቱን ሊያወርስ የቅዱሳንንም እንባ ከዓይናቸው ሊያብስ ኃጥአንን ሊወቅስ ጻድቃንን ሊያወድስ (ብሩካን ብሎ) መምጣቱን እያሰበች ቤተ ክርስቲያን ፈጣሪዋን ታመልካለች። ቅዱስ ያሬድም ይህንኑ ትምህርት በመዝሙሩ ጠቅሶ ስለዘመረውና በዚህ ቀንም እንዲዘመር ስለተደረገ ዕለቱ በባለዜማው ይትበሃል ደብረ ዘይት ይባላል።

4ኛው ሳምንት፦ መፃጉዕ

ይህ ዕለት የዓቢይ ጾም አራተኛ ሰንበት ነው። ስሙም እንደ ቅዱስ ያሬድ የዜማ ስያሜ «መፃጉዕ» ይባላል። በዚህ ዕለት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሽተኞችን ስለማዳኑ፣ ተአምራትን ስለማድረጉ፣ ጎባጣዎችን ስለማቅናቱ፣ ለምጻሞችን ስለማንጻቱ፣ ስለ መለኮታዊ ማዳኑ እና ታምራት ይመለካል።  To Read More

3ኛው ሳምንት፦ ምኩራብ

ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ዕለት ጌታ በመዋዕለ ትምሕርቱ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው።

ምኩራብ ምንድን ነው? የአይሁድ የጸሎት ቤት ነው። በብሉይ ዘመን የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም በነበረዉ ቤተ መቅደስ በሥርዐቱ የተመሠረተ ነበር ። ናቡከደነፆር  ግን ቤተ መቅደሱን አፈረሰ ፤ ሕዝቡን ወደ ባቢሎን አፈለሰ፤  ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚገኙባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎትና ለማሕበርተኛነት ልዪ ቤት መስራት እንደጀመሩ ይገመታል ። ሕዝ 11፣16 በክርስቶስ ጊዜ በእስራኤል ሐገር በየቦታው በኢየሩሳሌምም ብዙ ሙክራቦች ነበሩ።

ሐዋርያትም አይሁድ በተበተኑባቸዉ ቦታዎች ሲዘዋወሩ አስቀድመው ወደ ምኩራብ ገብተዉ ወንጌልን ያስተምሩ ነበር። ማቴ 4፣23 ሐዋ 6፣9  13፤5-14 Continue reading 3ኛው ሳምንት፦ ምኩራብ

የኪዳነ ምሕረት ንግስ በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤ/ክርስቲያን February 22, 2015

Medhanialem church Minnesota kidaneኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ቃል ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል እና፡፡

ዐብይ ጾመ

እንኳን እግዚአብሔር አምላክ ለዚህ ታላቅ ጾም በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

ይህንን ጾም በእስር ቤት ላሉት ለታመሙት ለተጨነቁት ወገኖቻችን እግዚአብሔር  የቸርነቱን ሥራ ይሰራላቸው ዘንድ በፀሎት ፤በሐሳብ ከእነሱ ጋር እንድንሆን እግዚአብሔር ይርዳን ጾሙንም የኀጢአት መደምሰሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግስተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን።

ዐቢይ የሚለው ቃል ዐብየ ከፍ ከፍ አለ ከሚለዉ የግዕዝ ግስ የወጣ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ታላቅ ማለት ነው፤ ይህንን ጾም አባቶቻችን በተለያየ ስያሜ ጠርተውታል፣ ጌታ እራሱ የጾመው ስለሆነ የጌታ ጾም በመባል ይጠራል በጾሙም ወቅት ሦስቱ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም ትዕቢት፣ ስስት፣ ፍቅረ ነዋይ ድል ተመተውበታል ጾሙም ብዙ መንፈሳዊ በረከት ስለምናገኝበት ጾመ ሁዳዴ በመባልም ይጠራል።

ጾሙ በድምሩ 55 ቀን ይጾማል ጌታ የጾመው 40 ቀን አይደል? ለምን 55 ሆነ ቢሉ Continue reading ዐብይ ጾመ