Category Archives: events

እንዳያመልጣችሁ! የበገና ምሽት ቅዳሜ ኤፕሪል 13, 2024 በሚኒስታ ደብረስላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አዳራሽ

ታላቅ የበገና ምሽት

በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ታዳጊ እና ወጣቶችተዘጋጅቶ ይቀርባል::

መቼ : ሚያዝያ 5, 2016 ዓ.ም. (April 13, 2024) ከቀኑ 4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ

እንዳያመልጣችሁ!
አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

በአብይ ጾም ውስጥ ያሉ ሳምንታት ስያሜ

የተከበራችሁ የቤተክርስትያናችን አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤
እንኳን ለ2016 ዐብይ ጾም አደረሰን!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለጾም ሥርዓት እና ደንብ አውጥታ በዓመት ውስጥ ሰባት የአዋጅ አጽዋማት እንዳሉና ማንኛውም ክርስቲያን እነኝህን አጽዋማት እንዲጾሙ ታዛለች። ከነዚህም አንዱ እና ታላቁ ጾም ዛሬ ሰኞ መጋቢት 2/2016 (March 11, 2024) የጀመርነው የአብይ ጾም ነው:: ለዚህም ቤተክርስቲያናችን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቷን ትገልጻለች።

ዐቢይ ጾም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ የጾመው ጾም እና ለእኛ አራያ የሆነበት ጾም ነው። እኛም እንድንጾማቸው በቤተ ክርስቲያናችን ከታዘዝናቸው ሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው። እኛ ምእመናን ጌታችን ያደረገውን ምሳሌ ተከትለን ጾሙን በየዓመቱ እንጾመዋለን። ዐቢይ ጾም ስምንት ሳምንታት (፶፭ ቀኖች) ሲኖሩት በውስጡ ስምንት ቅዳሜዎች፣ ሰባት እሑዶች ይገኛሉ።እነዚህም ዐሥራ አምስት ቀናት ሲሆኑ በእነዚህ ቀናት ከጥሉላት እንጂ ከእህል ውኃ ስለማይጦሙ እነዚህ ቀናት ሲቀነሱ የጦሙ ወራት ዐርባ ቀን ብቻ ይሆናል።

ዓብይ ጾም የተባለበት ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ስለሆነና ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎችን ድል የተነሱበት በመሆኑ ዛሬም ክርስቲያኖች የአምላካችንን አርአያ ተከትለን ሰይጣንን ድል የምንነሳበት ጾም ስለሆነ ነው።

የዐብይ ጾም በተለያዩ ስሞችም ይጠራል

  • ሁዳዴ ጾም ይባላል። ይህም የመንግሥት እርሻ ወይም ማንኛውም የሕዝብ ብዛት ያለበት ሥፍራ ሁዳድ ይባላል። በመሆኑም ዐቢይ ጾምም ከአጽዋማት ሁሉ ብዙ ቀናት ስለሚጾምና ክርስቲያኖች የሆኑ ምዕመናን ሁሉ ስለሚጾሙት የሁዳዴ ጾም ተባለ።
  • ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ፵ ቀን ስለሆነ ጾመ ዐርባ ም ይባላል /ማቴ.፬፥፩/

በአብይ ጾም ውስጥ ያሉ ሳምንታት ስያሜ

  • ዘወረደ
  • ቅድስት
  • ምኵራብ
  • መጻጕዕ
  • ደብረዘይት
  • ገብርኄር
  • ኒቆዲሞስ
  • ሆሳዕና
  • ትንሳኤ ናቸው ::

የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በአብይ ጾም ያላት የአገልግሎት መርኃ ግብር

  • ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 6 ኤ.ኤም እስከ 10 ኤ.ኤም የኪዳን ፀሎት አገልግሎት ይሰጣል።
  • ዘወትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 6 ኤ.ኤም እስከ 8 ኤ.ኤም የኪዳን ፀሎት ይደርሳል።
  • ዘወትር እሁድ ከንጋቱ 3 ኤ.ኤም ጀምሮ የፀሎት፣ የክርስትና፣ የቅዳሴ አገልግሎቶች ይሰጣል::

ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተካፊይ እንዲሆኑ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአገልግሎት ቀን መቁጠሪያ ::

  • የዓብይ ጾም (የሁዳዴ ጾም) :- ከመጋቢት 2 አስከ ሚያዝያ 27 (Monday March 11, 2024 – Sunday May 5, 2024)
  • መጋቢት መድሐኔዓለም :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : መጋቢት 29, 2016 (Sunday Apr. 7, 2024) / Megabit Medhanealem / The original Crucifixion.
  • ደብረ ዘይት :- መጋቢት 29, 2016 (Sunday April 7, 2024) / Debrezeit
  • ሀሳዕና :- ሚያዝያ 20, 2016 (Sunday April 28, 2024) / Hosanna
  • ሰሙነ ሕማማት :- ሚያዝያ 21, 2016 እስከ ሚያዝያ 26, 2016 (Monday April 29, 2024 to Friday May 3, 2024) / Holy/Passion week.
  • ጸሎተ ሐሙስ :- ሚያዝያ 25, 2016 (Thursday May 2, 2024) / Maundy Thursday
  • ስቅለት :- ሚያዝያ 26, 2016 (Friday May 3, 2024) / Good Friday (Crucifixion)
  • ትንሣኤ :- ሚያዝያ 27, 2016 (Sunday May 5, 2024) / Easter Sunday

በዚህ አብይ ጾም ሁላችም ስለሀገራችን እና ስለ ቅድስት ቤተክርስትያናችን አብዝተን የምንጸልይበት እኛም በረከት የምናገኝበት በስጋ ወደሙ የምንከብርበት ያድርግልን::

ጽሁፉን ያዘጋጀችው ወይዘሮ ሐና ስዩም ነች::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

የየካቲት ኪዳነምሕረትን የዋዜማ አገልግሎት እና በዓለ ንግስ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ!

በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን እንኳን ለየካቲት ኪዳነምሕረት በዓለ ንግስ በስላም አደረሳችሁ እያለች፣ የፊታችን ቅዳሜ የካቲት 16, 2016 ከቀኑ 4:00ፒ.ኤም. ጀምሮ (Saturday Feb. 24, 2024 from 4:00 pm) በዋዜማ፣ ቀጥሎም እሁድ የካቲት 17, 2016 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ (Sunday Feb. 25, 2024 from 2:00 am) በማህሌት የየካቲት ኪዳነምሕረትን በዓለ ንግስ በደመቀ ሁኔታ ታከብራለች:: በእለቱም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታቀርባለች::

መቼ? / When?
የዋዜማ አገልግሎት፣
ቅዳሜ የካቲት 16, 2016 ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ (Saturday Feb. 24, 2024 from 4:00 pm)
በዓለ ንግስ
እሁድ የካቲት 17, 2016 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ (Sunday Feb. 25, 2024 from 2:00 am)

ፎቶግራፉ የሚያሳየዉ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች በዚህ አመት የጥምቀት በአል አከባበር መርኃግብር ላይ ነዉ::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ

Click Here to Follow Us On Facebook

የዘንድሮው የከተራ እና ጥምቀት በዓል አከባበር እና የሃያ ሰባት አመቱ ቤዛኩሉ

በዚህ አመት የከተራ እና ጥምቀት በዓላት  ቅዳሜ ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016) እና እሁድ ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111 በሚገኘው ቦታ እንደወትሮው በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል:: የዘንድሮውን የጥምቀት በአል አከባበር ደማቅ እና ልዩ ያደረገው ነገር ቢኖር የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ለመጀመሪያ ጊዜ በመሀከላችን ተገኝተው ቡራኬ መስጠታቸው እንዲሁም የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች በብዛት ሆኖ በመሳተፍና ያቀረቧቸው ልዩ ልዩ መዝሙራት እና ሌሎች መንፈሳዊ ዝግጅቶች በልዩ ሁኔታ የሚጠቀሱ ናቸው ::

በተለያዩ ምክንያቶች የበዓሉን አከባበር መርኃግብር በቦታው በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ ለመሆን ላልቻላችሁ ሁሉ ይጠቅማል በማለት የቤዛ ኩሉ ሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች የሚዲያ ዝግጅት ክፍል ያካፈለንን ፎቶግራፎች ከዚህ በታች አቅርበናል::

የደብራችንን ታላቅነት ባገናዘበ መልኩ የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶችም ላቀረቧቸው መዝሙራት ፣ ልዩ መንፈሳዊ እና ትምህርታዊ ዝግጅቶች በተጨማሪም ላሳያችሁት መልካም አርአያዊነት ተግባር እያመሰገንን የደከማችሁበት ሁሉ ስለተሳካላችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን:: በዚህ አጋጣሚም  በደብራችን ውስጥ ለሚከናወኑት የሰንበ ት/ቤትና የልጆች ፕሮግራም ተሳታፊዎች: ካህናት: ፕሮግራም መሪዎች: አስተማሪዎች እና ወላጆች ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን። በተጨማሪም የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች የሚዲያ ዝግጅት ክፍልን ለፎቶግራፎቹ እጅግ በጣም እናመሰግናለን::

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
January 24, 2024
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ከተራ እና ለብርሀነ ጥምቀቱ በስላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ከተራ እና ለብርሀነ ጥምቀቱ በስላም አደረሳችሁ እያለች የፊታችን ቅዳሜ ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016) ከቀኑ 3 ፒኤም ጀምሮ የከተራ ጉዞ ወደ 6202 Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111 ይደረጋል:: ቀጥሎም እሁድ ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) ከቀኑ 1 ኤኤም ጀምሮ በማህሌት: ከቀኑ 5 ኤኤም በቅዳሴ እና ቀጥሎም በታቦት ሽኝት የብርሀነ ጥምቀት በአልን በደመቀ ሁኔታ ቤተክርስቲያናችን ታከብራለች::

በእለቶቹም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

የጥምቀት በአል የሚከበርበት አድራሻ: 6202 Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111
ስለ ከተራ እና ጥምቀት አከባበር መርኃ ግብር የሚከተለዉን ይመልከቱ!

የጥምቀት ጾም (የጋድ ጾም) :- ጥር 10, 2016 (Friday Jan 19, 2024)
ከተራ :- ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016)
ጥምቀት :- ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) / The Baptism of Christ (Epiphany).

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ
January 14, 2024
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በስላም አደረሳችሁ!

በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በስላም አደረሳችሁ እያለች የፊታችን ቅዳሜ ታህሳስ 27, 2016 (Saturday January 6, 2024) ከቀኑ 5 ፒኤም ጀምሮ በማህሌት: ቀጥሎም ከምሽቱ 11 ፒኤም ጀምሮ በቅዳሴ የእየሱሰ ክርስቶስን የልደት በአል በደመቀ ሁኔታ ታከብራለች:: በእለቱም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታቀርባለች::

መቼ: ቅዳሜ ታህሳስ 27, 2016 ከ 5 ፒኤም ጀምሮ
When: Saturday January 6, 2014 from 5pm

ከዚህ በታች ያሉት ፎቶግራፎች የሚያሳዩት የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የ2016 ዓ.ም. የእየሱሰ ክርስቶስ የልደት በአልን በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያናችን ውስጥ ሲያከብሩ ነዉ::

የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ ከተመሰረተ 27 አመት አስቆጥሯል::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም): ቅዳሜ ኅዳር 15 ለሚጀመረው እና በረከት ለምናገኝበት ጾመ ነቢያት እንኳን አደረሰን!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

የተከበራችሁ የቤተክርስትያናችን አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤
እንኳን ለጾመ ነቢያት (የገና ጾም) በሠላም አደረሳችሁ።

የኢትዮያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰባት የአዋጅ አጽዋማት ያሏት ሲሆን ከእነዚህ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የነቢያት ጾም ነው። ጾሙን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከመገለጡና ሰው ከመሆኑ በፊት ነቢያት የጌታን መምጣት በናፍቆት በጾምና በጸሎት ሲጠባበቁ ነበር። ስለዚህ የነቢያትን የጾም ድካም ለማሰብና እንደ ነቢያት መንፈስ ኃይልን ለመልበስ በእምነት ለመጽናት ኃጢአትን ለመዋጋት ሲባል ይህን ጾም እኛ እንጾመዋለን።

ይህንን ጾም በተመለከተ በፍትሐ ነገሥት (ፍትሕ መንፈሳዊ) አንቀጽ ፲፭፥፭፻፷፬ ጀምሮ ተጽፏል። በፍትሕ መንፈሳዊ በአንቀጽ ፲፭፥፭፻፷፰ ላይ እንደተገለጸው ከኅዳር እኩሌታ እስከ ልደት የሚጾመው ጾም ነው።
“መጀመርያው የኅዳር እኩሌታ፡ ፋሲካው፡ የልደት በዓል ነው።” ተብሎ የጾመ ነቢያት መነሻውና መድረሻውን ፍትሐ ነገስት ላይ ተገልጿል። ይህም ማለት በሦስቱ ወንጌላውያን ማለትም በዘመነ ማቴዎስ፣ በዘመነ ማርቆስና በዘመነ ሉቃስ የገና ጾም ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ  በኅዳር ፳፱ ይፈሰካል። በዚህ በያዝነዉ በዘመነ ዮሐንስ ደግሞ የገና ጾም ቅዳሜ ኅዳር ፲፭  ተጀምሮ እሁድ ኅዳር ፳፰
ይፈሰካል።

ጾሙን የበረከት ያድርግልን!

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) :-
ከህዳር 15,2016 አስከ ታህሳስ 28, 2016
(Saturday Nov 25, 2023 – Sunday Jan 7, 2024)

ጽሁፉን ያዘጋጀችው ወይዘሮ ሐና ስዩም ነች::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

የኅዳር ሚካኤልን በዓለ ንግስ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ!

የኅዳር ሚካኤል በዓለ ንግስ እሁድ ህዳር 9, 2016 በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ ይከበራል:: መጥተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች::

መቼ? / When?
እሁድ ህዳር 9, 2016 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ
Sunday Nov. 19, 2023 from 2:00 am

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406 ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
Website: https://www.debreselam.net

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ / Click Here to Follow Us On Facebook

የ2016 የአመታዊ፣ የንግሥ በዓላት እና የአጿማት ቀን መቁጠሪያ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን

የተከበራችሁ የቤተክርስትያናችን አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤
የ2016 አ.ም. ከገባ የመጀመሪያውን ወር አገባድደናል:: አዲስ አመት እንደመሆኑም የአመታዊ፣ የንግሥ በዓላት እና የአጿማት ቀን አቆጣጠሩ ላይ ብዙ ማወቅ የምትፈልጉት እንዳሉ እንገነዘባለን:: ለምሳሌም ያህል የጾም ቀኖች እና ወራቶች የትኞቹ ናቸዉ? የአመታዊ እና የንግሥ በዓላት የሚዉሉባቸዉ ቀኖችስ የትኞቹ ናቸዉ? በዩኤስ ባንክ ስታዲየም ለአዲስ ቤተክርስቲያን ማሰሪያ የሚውል የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ቀኖች እና ወራቶችስ የትኞቹ ናቸዉ? የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት የህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶች አገልግሎት መርኃ ግብሮች መቼ መቼ ሊውሉ እንደሚችሉ እቅድ እና ፕሮግራም ወጥቶላቸዋል? ይህ
የቀን መቁጠሪያ ለእነዚህ ጥያቄዎች መልሰ ይሰጣል:: ስለሆነም ከወዲሁ በመዘጋጀት ከመላዉ ቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተካፊይ እንዲሆኑ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

  • ማሕሌተ ጽጌ / ወርሃ ጽጌ (የፍቃድ ጾም ነው) : ከመስከረም 26, 2016 እሰከ ህዳር 6, 2016 (Sat Oct 7, 2023 – Thurs Nov 16, 2023)
  • የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በዩኤስ ባንክ ስታዲየም :- ጥቅምት 12, 2016 (Mon Oct 23, 2023) / U.S. Bank Stadium volunteer work
  • መንፈሳዊ ጉባኤ :- ጥቅምት 17, 2016 (Saturday Oct 28, 2023) ከ3:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ. በጉባኤ አዳራሽ 1040 Osborne Road NE, Fridley MN 55432)
  • መንፈሳዊ ጉባኤ :- ጥቅምት 18, 2016 (Sunday Oct 29, 2023) ከ4:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • መንፈሳዊ ጉባኤ :-ጥቅምት 22, 2016 (Thursday Nov 2, 2023) ከ5:00 ፒ.ኤም.. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • መንፈሳዊ ጉባኤ ;_ ጥቅምት 24, 2016 (Saturday Nov 4, 2023) ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • ጥቅምት መድሐኔዓለም :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : ጥቅምት 25, 2016 (Sunday Nov 5, 2023)
  • የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በዩኤስ ባንክ ስታዲየም :- ኅዳር 2, 2016 (Sunday Nov 12, 2023) / U.S. Bank Stadium volunteer work 
  • ኅዳር ሚካኤል :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : ህዳር 9, 2016 (Sunday Nov. 19, 2023) / Hidar St. Michael
  • ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) :- ከህዳር 15,2016 አስከ ታህሳስ 28, 2016 (Saturday Nov 25, 2023 – Sunday Jan 7, 2024)
  • የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በዩኤስ ባንክ ስታዲየም :- ኅዳር 17, 2016 (Monday Nov 27, 2023) / U.S. Bank Stadium volunteer work
  • የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በዩኤስ ባንክ ስታዲየም :- ታኅሳስ 14, 2016 (Sunday Dec 24, 2023) / U.S. Bank Stadium volunteer work
  • ታኅሳስ ገብርኤል :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : ታኅሳስ 21, 2016 (Sunday Dec. 31, 2023) / Tahisas St. Gabriel
  • የበጎፈቃደኝነት አገልግሎት በዩኤስ ባንክ ስታዲየም :- ታኅሳስ 21, 2016 (Sunday Dec 31, 2023) / U.S. Bank Stadium volunteer work
  • የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት የልጆች የገና በዓል ዝግጅት :- ታኅሳስ 26, 2016 (Friday Jan 5, 2024)
  • ልደት (ገና) :- ታኅሳስ 28, 2016 (Monday Jan 7, 2024) / The Birth of Christ
  • የጥምቀት ጾም (የጋድ ጾም) :- ጥር 10, 2016 (Friday Jan 19, 2024)
  • ከተራ :- ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016)
  • ጥምቀት :- ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) / The Baptism of Christ (Epiphany).
  • የካቲት ኪዳነምሕረት :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : የካቲት 17, 2016 (Sunday Feb. 25, 2024) / The Covenant of Virgin Mary.
  • ጾመ ነነዌ :- የካቲት 18, 2016 (Monday Feb 26, 2024)
  • የዓብይ ጾም (የሁዳዴ ጾም) :- ከመጋቢት 2 አስከ ሚያዝያ 27 (Monday March 11, 2024 – Sunday May 5, 2024)
  • መጋቢት መድሐኔዓለም :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : መጋቢት 29, 2016 (Sunday Apr. 7, 2024) / Megabit Medhanealem / The original Crucifixion.
  • ደብረ ዘይት :- መጋቢት 29, 2016 (Sunday April 7, 2024) / Debrezeit
  • ሀሳዕና :- ሚያዝያ 20, 2016 (Sunday April 28, 2024) / Hosanna
  • ሰሙነ ሕማማት :- ሚያዝያ 21, 2016 እስከ ሚያዝያ 26, 2016 (Monday April 29, 2024 to Friday May 3, 2024) / Holy/Passion week.
  • ጸሎተ ሐሙስ :- ሚያዝያ 25, 2016 (Thursday May 2, 2024) / Maundy Thursday
  • ስቅለት :- ሚያዝያ 26, 2016 (Friday May 3, 2024) / Good Friday (Crucifixion)
  • ትንሣኤ :- ሚያዝያ 27, 2016 (Sunday May 5, 2024) / Easter
  • የእመቤታችን ልደት በአል :- ግንቦትt 1, 2016 (Thursday May 9, 2024) / The Birthday of Virgin Mary
  • የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት ለህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶች የሰመር ኮርስ :- ሰኔ 10,-ሰኔ 21 2016 (June 17, 2024 – June 28,2024) / Kids summer course
  • እርገት :- ሰኔ 6, 2016 (Thursday June 13, 2024) / Ascension. The day of Holy Spirit (Pentecost)
  • ሰኔ ሚካኤል :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : ሰኔ 9, 2016 (Sunday June 16)/ Sene St. Michael.
  • ጴራቅሊጦስ :- ሰኔ 16, 2016 (Sunday June 23, 2024) / Peraklitos
  • ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) :- ከሰኔ 17, 2016 እሰከ ሀምሌ 5, 2016 (Monday June 24, 2024 – Friday July 12, 2024)
  • ጾመ ድህነት :- ሰኔ 19, 2016 (Wednesday June 26, 2024)
  • በአለ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወገብረመንፈስ ቅዱስ (አቦ በአል) :- ሐምሌ 5, 2016 (Friday July 12, 2024) / The Martyrdom of Peter and Pau
  • የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት የልጆች ሰመር ካምፕ :- ከሀምሌ 8, 2016 እስከ ሀምሌ 12, 2016 (Monday July 15, 2024 – July 19, 2024) / kids summer camp
  • የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት የህፃናት ከ12 አመት በታች የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ :- ሐምሌ 18, 2016 (Thursday July 25,2024) / Field Trip for children under 12 years old
  • ሐምሌ ገብርኤል :- በዓለ ንግሱ መርኃ ግብር የሚከናወንበት ትክክለኛ ቀን : ሐምሌ 21, 2016 (Sunday July 28, 2024) /  Hamle St. Gabriel.
  • የቤዛ ኩሉ ስንበት ት/ቤት የታዳጊና የወጣቶች (teenagers ) ከ13 አመት በላይ የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ :- ሐምሌ 20, 2016 (Saturday July 27, 2024) / Field Trip for youth over 13 years old
  • ጾመ ፍልሰታ :- ከነሀሴ 1, 2016 እስከ ነሀሴ 16, 2016 (Wed August 7, 2024 – Thursday Aug 22, 2024)
  • ደብረ ታቦር :- ነሐሴ 13, 2016 (Monday August 19, 2024) / Transfiguration (Debre Tabor)
  • ነሐሴ ኪዳነምሕረት :- ነሐሴ 16, 2023 (Thursday August 22, 2024) / The assumption of Virgin Mary.

ለዚህ የቀን መቁጠሪያ ዝግጅት መሳካት የተባበሩኝን ወይዘሮ ሀና ስዩምን: አቶ ደረሰ ለማን እና አቶ ጌታቸው ደበበን አመስግኑልን:: እኛም እጅግ በጣም እናመሰግናለን::

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ
October 15, 2023
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ኢሜይል: membersservice@dsmachurch.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ይደረጋል!

  • መንፈሳዊ ጉባኤ :- ጥቅምት 17, 2016 (Saturday Oct 28, 2023) ከ3:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ. በጉባኤ አዳራሽ 1040 Osborne Road NE, Fridley MN 55432
  • መንፈሳዊ ጉባኤ :- ጥቅምት 18, 2016 (Sunday Oct 29, 2023) ከ4:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • መንፈሳዊ ጉባኤ :-ጥቅምት 22, 2016 (Thursday Nov 2, 2023) ከ5:00 ፒ.ኤም.. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • መንፈሳዊ ጉባኤ ;_ ጥቅምት 24, 2016 (Saturday Nov 4, 2023) ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
  • ጥቅምት መድሐኔዓለም :- ጥቅምት 25, 2016 (Sunday Nov 5, 2023) ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን

ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተካፊይ እንዲሆኑ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ
October 15, 2023
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ኢሜይል: membersservice@dsmachurch.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ለ፳፻፲፮ ጽጌ ማሕሌት በሠላም አደረሳችሁ። /October 7, 2023 – November 16, 2023/

የተከበራችሁ የቤተክርስትያናችን አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤
እንኳን ለማሕሌተ ጽጌ በሠላም አደረሳችሁ።
ፅጌ ማለት አበባ ማለት ሲሆን ፀገየ ከሚለው የግዕዝ ቃል የመጣ ነው። ጽጌ ማሕሌት በየአመቱ ከመስከረም ፳፮ እስከ ህዳር ፮ (Oct 7, 2023 – Nov 16, 2023)
፵ ቀናት ወይም ፩ ወር ከ ፲ ቀን የሚቆይ ነው። ጽጌ ማሕሌት እመቤታችን ጌታችንን ይዛ መሰደዷን መራቧን መጠማቷን በማሰብ ነው

በማሕሌተ ጽጌ ወቅት ያሉት ሳምንታት ውብ ናቸው ምክንያቱም :-
☞እማምላክን ከነልጇ እንለምንበታለን ስደቷን እናስብበታለን፣
☞ የእመቤታችንን ፍቅሯን እናትነቷን አማላጅነቷን ከሊቃውንቱ ጋር ሆነን በዝማሬ እናወድስበታለን ፣

ጽጌ ማሕሌት የፈቃድ ፆም ስትሆን ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች ብቻ ይፆሟታል። ምንም እንኳን ፆመ ፅጌ ከ ፯ ቱ የአዋጅ አፅዋማት መካከል ባትሆንም እና እንድንፆማት በአዋጅ ባንታዘዝም በፈቃዳችን በመፆማችን ከፆሟ ረድኤት በረከት የምናገኝባት ነች።

ሰንበትን ከጌታ ከኢየሱስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር ሌሊቱን በምስጋና በያሬዳዊ ዜማ ሳምንቱን ደግሞ በፈቃዳችን ማንም ሳያዘን የድንግል ማርያም ፍቅሯ አክብረን እንጾማለን።

እንኳን ለዚህ ጊዜ አደረሰን አደረሳችሁ !!!
የእመቤታችን ፍቅሯ ይብዛልን::

ጽሁፉን ያጠናቀረዉ አቶ ኤልያስ ወርቅህ ነዉ::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ኢሜይል: membersservice@dsmachurch.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

የደመራ በዓል ቅዳሜ መስከረም ፲፱, ፳፻፲፮ /September 30, 2023!

የ፳፻፲፮ ዓ.ም. የደመራ በዓል ቅዳሜ መስከረም ፲፱, ፳፻፲፮ (September 30, 2023) ከ 3 ፒ.ኤም. ጀምሮ በፌለን መናፈሻ በደመቀ ሁኔታ ስለሚከበር ከመላዉ ቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተካፊይ እንዲሆኑ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

አድራሻ? / Venue?
1600 Phalen Drive
St. Paul, MN 55106

ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ኢሜይል: membersservice@dsmachurch.com
Website: https://www.debreselam.net
Facebook: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስን በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

የዘንድሮዉ የነሐሴ ኪዳነ ምህረት በዓለ ንግስ በደመቀ ሁኔታ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይከበራል:: መጥተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

መቼ? / When?
ማነክሰኞ ነሐሴ 16, 2015 ከ2:00 ኤ.ኤም. ጀምሮ
Tuesday August 22, 2023 from 2:00 pm

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406

በፌስቡክ እንዲከተሉን ይህን ይጫኑ / Click Here to Follow Us On Facebook

የደብረ ታቦር ክብረ በዓልን በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያክብሩ

መቼ? / When?
ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ
Saturday August 19, 2023 from 4:00 pm

የዚህ ዓመት የደብረ ታቦር ክብረ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 13, 2015 (Saturday August 19, 2023) ከ4:00 ፒ.ኤም. ጀምሮ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ዝግጅትይከበራል። እርስዎም መጥተው የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ የቤዛ ኩሉ የሰንበት ትምህርት ቤት ጥሪውን ያቀርባል።

ደብረ ታቦር (Transfiguration- Debre Tabor)

ነሐሴንና ጳጉሜን የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የደብራችን አባላት የእንቅስቃሴ ወሮች እንዲሆኑ ስለማቀድ

በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም.ን መገባደጃ በመንተራስ በቀሪዎቹ የነሐሴና ጳጉሜ ወሮች የአዲስ የቤተክርስቲያን አባላት የትውውቅ ጊዜ እና የነባር የቤተክርስቲያን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብሮች እንዲታቀዱ የአስተዳደር ቦርዱ ወስኖ የሚከተሉት መርኅግብሮች እንዲከናወኑ ይሆናል:: አዲስ የቤተክርስቲያን አባል ማለት በኢትዮጵያ አቆጣጠር የ2015 ዓ.ም የደብራችን አባል የሆኑ ማለት ነው::

የአዲስ አባላት የትውውቅ መርኅግብር:-

  1. እሁድ እሁድ ከቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ እታች አዳራሽ ውስጥ አዲስ የቤተክርስቲያን አባሎቻችንን የእንኳን የደብራችን አባል ሆናችሁ በማለት የካህናት የአስተዳደር ቦርድ እና የአባላት ማኅበራት ተወካዮች ጋር ትዉዉቅ ይደረጋል::
  2. የእዲስ አባላት ስም ዝርርዝም እታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው ቴሌቪዥን ስኪሪን ላይ ይተላለፋል::
  3. የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ ላልወስዱ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  4. በእለቱም ለ ዲስ አባላት ቡና ሻይና ዳቦ ካለ ይቀርባል::

የነባር የደብራችን አባላት እንቅስቃሴ መርኅግብር:-

  1. ነባር የቤተክርስቲያን አባሎች እሁድ እሁድ አታች አዳራሽ ውስጥ በሚገኘው የቦርድ አባላት የጠረጴዛ ቢሮ ድረስ በመሄድ የአባላት መዝገብ ላይ ያለው አድራሻችሁ ስልክ ቁጥራችሁና ኢሜል ትክክል እንደሆነ እንድታረጋግጡልን በአክብሮት እንጠይቃለን::
  2. የደብራችን አባልነት አዲስ መታወቂያ ካርድ ያላወጡ በእለቱ የቤተክርስቲያን አባልነት መታወቂያ ካርድ እንዲያወጡ ይደረጋል::
  3. የየደብራችን አባልነት የወርሀዊ መዋጮአችሁ መጠናቀቁን የቦርድ አባላትን መጠየቅና ውዝፍ ካለ በወቅቱ እንዲጠናቀቅ መሞከር
  4. የደብራችን አባል ያልህኑ ዘመዶች ጏደኞች እና ወዳጆችን የቤተክርስቲያኗ አባል እንዲሆኑ ማነቃቃትና ማበረታታት
  5. የቤተክርስቲያናችን የመረዳጃ ማህበር አባል ለመሆን መሞከር
  6. ገቢው ለአዲስ ቤ.ክ. ማስሪያ የሚውል የበጎፍቃድ ስራ አገልግሎት ላይ ለመሳተፍ ከፕሮግራሙ እስተባባሪ ከዶ/ር አሻግሬ መረጃ መጠየቅ

መርኅግብሮቹ ከመጪው እሁድ የቅዳሴ አገልሎት ፍፃሜ በሗላ ለአምስት ተከታታይ እሁዶች የምንከታተላቸው ይሆናል:: ቀኖቹም ነሐሴ7(Sug 13), ነሐሴ14(Aug 20), ነሐሴ21(Aug 27), ነሐሴ28(Sep 3), ጳጉሜ5(Sep 10) ናቸው::

ያቀድናቸውና ያሰብናቸው እንዲሳኩ ውድ የደብራችን ነባርና አዲስ የቤተክርስቲያን አባላት ከምንጊዜውም በበለጠ ሁኔታ የሰበካ ጉባዔውን እንድትተባበሩት በትህትና እንጠይቃለን:: በፅሁፍም ሆነ የመረጡትን የሰበካ ጉባዔ አባል በግል በመቅረብ አዳዲስ የአሰራር ሃሳቦችን እንድታካፍሉን ይሁን::

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች እንኳን ደስ ያላችሁ ! / Congratulations to 2023 Grads & Families!

“ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ” መዝ.118:26

በዘንድሮው የ2023 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍልን እና የከፍተኛ ትምህርትን ላጠናቀቁ የቤተክርስቲያናችን ወጣቶች የእንኳን ደስ ያላችሁ የምስክር ወረቀት ቤተክርስቲያናችን ባለፈው እሁድ ሐምሌ 30 (Aug 6, 2023) አበርክታለች:: የሚቀጥለው የትምህርትና የመደበኛ ስራ ዘመናቸውም የተቃና እንዲሆንላቸውም ከእግዚያብሔር ቤት ተመርቀዋል::

Congratulations to 2023 grads and families. Graduates were handed out congratulating certificates by our church during the Sunday church services on Aug 6, 2023.

የደብራችን 2023 ተመራቂ ተማሪዎች እና ቤተሰቦች በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ !

Church Members Meeting is Scheduled for July 2, 2023 / የቤተ ክርስቲያን አባላት ስብሰባ በመጪዉ እሁድ ሰኔ 25 2015

በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአባላት ስብሰባ በመጪዉ እሁድ ሰኔ 25 2015 (July 2nd, 2023) ይደረጋል:: ስብሰባው የቅዳሴ አገልግሎት እንደተጠናቀቀ ስለሚጀመር ፤ እባክዎ የስብሰባዉ ተካፊይ እንዲሆኑ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota will hold all church members meeting on July 2, 2023 after Sunday church services. Please attend.

Nineth Annual 5K Run and Walk Scheduled for July 1st, 2023 @ Phalen Park, St Paul, MN.

በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 9ኛውን የ5000 ሜትር ሩጫና እርምጃ መርኃ ግብር በመጪዉ ቅዳሜ ሰኔ 24 2015 (July 1st, 2023) አዘጋጅቷል፤

Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Minnesota will hold its 9th annual 5K run and walk on July 1st, 2023 @ Phalen Park, St Paul, MN. Please mark your calendar.

Registration Fee: $25 / person

Race Venue/Address 
Phalen Park 
1600 Phalen Dr.
St. Paul MN 55106

Start Time: 7:30 AM
End Time:  12:00 PM

Race T-shirt Pickup at Phalen Park on the race day.

Registration Form – Age Groups 15 to 30 and above 30 years old.
Award: Male & Female by age groups.
      1st Place : Medal and Certificate
      2nd Place : Medal and Certificate
      3rd Place : Medal and Certificate

Contact for more information: Heyente Senay 612-554-2195