Category Archives: Uncategorized

የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ – ሐምሌ 19, 2007

በሰሞነ ህማማት ያውም በፀሎተ ኃሙስ ማውገዝ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮት የጣሰና ኢቂኖናዊ ነው ተባለ

የቤተ ክርስቲያኗ ምዕመናን የመልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ስብከት በዲቪዲ ተባዝቶ ለወደፊትም ለታሪክ ማጣቀሻ ይረዳ ዘንድ አንዲቀርብላቸው በጠየቁት መሰረት ከእሁድ ነሐሴ 28 2007 ወይንም July 5, 2015 ጀምሮ ለደብሩ መዕመናን ያከፋፈልን ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ እውነታውን በአለም ላይ የተበተነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ይረዳው ዘንድ በደብሩ ድረ ገጽ፣ ፊስቡክ አካውንት አንዲሁም በሌሎች ድረ ገጾች እንለቃለን።

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳትሆን በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያዊነት የሚንጸባረቅባት የኃይማኖት ተቋም በመሆኗ፣ በዘር፣ በቋንቋ ፣ እንዲሁም በጐጥ ያልተከፋፈለች ስለነበረች በኃይማኖት ሽፋን ለረዥም አመታት አብሮ የኖረን ህዝብ በዕለተ ሆሳዕና ለምን ቀደሳችሁ ብሎ በካህናቱ ላይ በሰሞነ ህማማት ያውም በፀሎተ ኃሙስ በአባ ዘካሪያስ የተላለፈው ውግዘት የቤተክርስቲያንን አስተምህሮት የጣሰና ኢቂኖናዊ መሆኑን መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ፍትሃ ነጋስትን በማጣቀስ እስተምረዋል። በመቀጠልም በሰሞነ ህማማት እንኳን ውግዘት ማውገዝ ይቅርና ይፍቱህ መባል እንኳን በተከለከለበት ጊዜ ያውም በፀሎተ ሀሙስ ለካህናቱ የውግዘት ደብዳቤ መስጠት የቤክርስቲያንን ህግ የጣሰ፣ ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቅ፣ ወደፊትም የማይታይ መሆኑን ለተሰበሰበው ምዕመናን አስረድተዋል። የምስልና የድምጽ ዝርዝር መልዕክቱን ከቪዲዮው ይመልከቱ

የጸሎት አገልግሎት (Prayer Services)

Ethiopia

የፀሎተ ፍትኃት መርኃ ግብር በሊቢያ ለተሰውት ሰማዕታት

እሁድ April 26 2015 ከጠዋቱ 5AM  – 10 AM በፀሎትና በቅዳሴ

ከ10AM ጀምሮ በፀሎተ ፍትኃት ይታሰባሉ

 

ወቅታዊ መግለጫ:-       የሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሊቢያ  በሚገኙ የእምነታችን ተከታዮች ላይ ራሱን አይ ኤስ እያለ በሚጠራው አሸባሪ ቡድን የተፈጸመባቸውን ዘግናኝ እና አሳዛኝ ግድያ በጽኑ ታወግዛለች።  በቀደሙት ዘመናት አባቶቻችን ቅዱሳን ሰማእታት ስለ እምነታቸው ሲሉ፣ ስለ ክረስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለ ቤተክርስቲያን ሲሉ በአላውያን ነገሥታት እና አሕዛብ መከራን ተቀብለዋል፣በመጋዝ ተሰንጥቀዋል፣ በእሳት ተቃጥለዋል፣ በፈላ ውኃ ተቀቅለዋል። ደማቸውንም ስለመንግሥተ ሰማያት ሲሉ አፍስሰዋል። ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

ድንግል ሆይ በኃጢአት በፍትወት የተጸነስሽ አይደለሽም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!

እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ “መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው” ብሎ ልበ አምላክ ዳዊት በመዝሙሩ ስለዘመረላት፤ ዳግመኛም ቅዱስ ያሬድ “ማርያምሰ ተኀቱ  እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ- ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና በቅድስና በድንግልና ታበራለች)” Continue reading ድንግል ሆይ በኃጢአት በፍትወት የተጸነስሽ አይደለሽም

የትንሳኤ አገልግሎት

This will conclude our  live Streaming  for Easter, you may still able to view prerecorded Services. 

የህማማት አገልግሎት

Click the video for Good Friday’s Service 

Passed Recorded Live Services (ያለፉትን ዕለታት አገልግሎት ለማየት)

የፀሎተ ሐሙስ አገልግሎት April 9 ከጠዋቱ 5AM ይጀምራል (Maundy Thursday Services Start April 9th @ 5AM) ጸሎተ ሐሙስ፣ ሕፅበተ ሐሙስ፣ የምስጢር ቀንና የሐዲስ ኪዳን ይባላል። ጸሎተ ሐሙስ የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነት በጌታ ሴማኒ ሲጸልይ በማደሩ ነው(ማቴ 26፥36)።  ሕፅበተ ሐሙስ መባሉም የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ነው፤ የምስጢር ቀን መባሉ ከሰባቱ ምስጢረ ቤተ ክርስቲያን አንዱ ምስጢረ ቁርባን የተመሰረተበት ዕለት በመሆኑ ነው። የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ መባሉም መሥዋዕተ ኦሪት አልፎ የሐዲስ ኪዳኑ መስዋዕት ሊሰዋ በመሆኑ ነው። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው። (ሉቃ 22፥20)

የስቅለት አገልግሎት April 10 ከጠዋቱ 5AM ይጀምራል (Good Friday Services Start April 10th @ 5AM)

የመድኃኔዓለም ንግስና የሆሳዕና በዓል (Palm Sunday and our Savior’s Celebration)

PalmSunday30የመድኃኔዓለም ንግስና የሆሳዕና በዓል ብዙ ህዝብ በተገኘበት በደብረ ሰላም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ ተከበረ፤ አነሆ ስዕላዊ መግለጫውንና፤ ተስቀሳቃሽ ምስላዊ መግለጫውን  (Palm Sunday and our Savior’s Celebration at Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, here is the pictures &  video – 2015)

 

የመድኃኔዓለም ዓመታዊ ንግስና የሆሳዕና በዓል April 5, 2015

April 4, 2015 ዋዜማና ስብከት በተጋባዣ እንግዳ ከ3PM ጀምሮ፤ እሁድ April 5 ማኅሌት፣ ቅዳሴና ስብከት ከ3:00AM ጀምሮ።

 ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው። ሆሣዕና አስቀድሞ ካለው ረቡዕ ጀምሮ የሚታሰብ ታላቅ የቤተክርስቲያን የበዓል ቀን Continue reading የመድኃኔዓለም ዓመታዊ ንግስና የሆሳዕና በዓል April 5, 2015

7ኛው ሳምንት፦ ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው። በዚህ ዕለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን  ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሦስት ላይ ያለውን ስለዘመረው የዕለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል።

የስብሰባ ጥሪ/General Assembly Meeting

የፊታችን እሁድ March 22, 2015 ከቅዳሴ በኋላ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ስለምናደርግ በዕለቱ ተገኝተው የስብሰባው ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። በዕለቱም ቤተ ክርስቲያኗ ምሳ አዘጋጅታ ትጠብቅዎታለች፤ የሰማ ላልሰማ ያሰማ፤ “ትቀሩና ማርያምን እንጣላችኋለን” ይላሉ የሰበካ ጉባኤው አባላት። (Debreselam Ethiopian orthodox Tewhaedo Church will be holding a General Assembly Meeting on Sunday March 22, 2015 right after a Church Service (Liturgy).

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የአስተዳደር ቦርድ (DSMA Board of Trustees)

የኪዳነ ምሕረት ንግስ ዝማሬ


ጾመ ነነዌ /Tsome Nenewe((The fast of Nineveh)

ጾመ ነነዌ – ሰኞ ጥር 25, 2007 ይጀምራል Tsome Nenewe (The fast of Nineveh): 3 days fasting which starts on the Monday proceeding before Abye Tsome (Lent) – Start on Monday February 02, 2015 – 04, 2015

Abye Tsome or Hudade (Lent): 55 days Fasting before Easter which is divided in to the following three categories: – Lent start on February 16, 2015

  • Tsome Hirkal: 8 days fasting which starts 8 days proceeding before Tsome Arba.
  • Tsome Arba: 40 days fasting which starts immediately after Tsome Hirkan up to Palm Sunday.
  • Tsome Himamat: 7 days fasting which starts on the Monday after Palm Sunday until Easter

ጥምቀት ምንድን ነው? ለምንስ እንጠመቃለን?

TimketHannaጥምቀት “አጥመቀ” ከሚለው የግእዝ ቃል/ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም በውኃ ውስጥ መዘፈቅ ወይንም መነከር ማለት ነው። ጥምቀት ከጌታችን እና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት በፊትም የነበረ ሰዎች ከህመማቸው ፈውስ የሚያገኙበት ማለትም የሥጋ ድህነት ከሚገኝበት የፈውስ መንገዶች አንዱ ነበረ። Continue reading ጥምቀት ምንድን ነው? ለምንስ እንጠመቃለን?

Epiphany/በዓለ ጥምቀት

Gehad Fasting – የጥምቀት ፆመ ገሃድ(ጋድ) – January 18, 2015 (ጥር 10, 2007) – This fasting is observed on the eve of Epiphany.

Epiphany Celebration On January 17, 2015 starting @ 3PM , Sunday Service Start @ 2AM –  (የጥምቀትን በዓል በደመቀ ሁኔታ በ2007 (2015) ለመጀመሪያ ግዜ  እናከብራለን )

Timket

ቅዳሜ – ስብከተ ወንጌል እና ዝማሬ – በተጋበዥ ሰባኪ መንጌል እና በተጋበዥ ዘማሪ ከ 5PM ጀምሮ 

እሁድ ከ 2AM – 7AM ማኅሌት 

ከ7AM – 10AM ቅዳሴ

ከ10AM – 12AM ስብከተ ወንጌልና ታቦታቱን ማክበር 

የበዓለ ጥምቀቱን በረከት መጥተሁ ይካፈሉ ዘንድ ቤ/ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች

የልደት ዝማሬ

የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደተ በዓል አከባበር በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ

Christmas2015_6የዘንድሮው የ2007 ዓ.ም የልደት በአል በደብራችን ከመቼውም ጊዜ ለየት ባለና በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል። ለበአሉ ልዩ ድምቀት ከሰጡት ጉዳዮች አንደኛው በቀርቡ ደብራችንን የተቀላቀሉ አዳዲስ ካህናት የቤተክርስቲያንን ትምህርት በተለይም የማኅሌት አገልግሎት ሙያ ያላቸውና ሁለገብ እውቀትን የተላበሱ መሆናቸው ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ምንም እንኳን በእለቱ ከባድ የአየር ቅዝቃዜ የነበረ ቢሆንም የቤተክርስቲያናችን አባላት ምእመናን ብርዱን ሳፈሩና ሳይሳቀቁ የጌታችንን የልደት በረከት ለመካፈል ቤተክርስቲያኗን አጨናንቀው መገኘታቸው ለበአሉ ልዩ ድምቀት ሰጥቶት አምሽቷል። Continue reading የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደተ በዓል አከባበር በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ

ልደተ ክርስቶስ

 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አኃዱ አምላክ፤ አሜን።

የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ በሐጢያት ከወደቀ በኋላ እግዚአብሔር ወደ ቀደመ ክብሩና ቦታው ይመልሰው ዘንድ በንሰሐ ወደፈጣሪው ቀረበ። አዳም እና ሔዋን ከገነት ከወጡ በኋላ ለአርባ ቀናት ያህል ሱባዔ ገብተው ሳለ በ35 ኛው ቀን ከግማሽ ላይ ቀድሞ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ እንዲያፈርሱ ያደረጋቸው ሰይጣን ዳግመኛ ወደ ሔዋን ቀርቦ ሔዋን ሆይ ጸሎታችሁ ተሰማ አዳምን ይዘሽ ወደዚህ ነይ አላት። Continue reading ልደተ ክርስቶስ

የገብርኤል ንግስ በደብረሰላም

 St. Gabriel Annual Celebration – December 28, 2014