በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. የልጆች ትምህርት አገልግሎት በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን

በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የሰንበት ት/ቤት የልጆች ትምህርት ክፍል አገልግሎት ዘርፈ ብዙ የሆኑ ልዩ ልዩ ትምህርታዊ እና ማህበራዊ አገልግሎቶች ይሰጣሉ:: ለመጥቀሰም ያህል:-
ዘወትር ቅዳሜ ከ1.00pm-6.00pm ለልጆች የበገና ትምህርት፣ የወንጌል ትምህርት፣ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት እና የአብነት (የድቁና) ትምህርት ይሰጣል።

የቅዳሜ ክፍለ ግዜ በአራት የትምህርት ዘርፍ አገልግሎት ያተኩራል::
1.00pm-3.00pm የበገና ትምህርት
1.00pm-3.00pm የወንጌል ትምህርት ልጆች በየእድድሜያቸው በሁለት ክፍሎች::
4.00pm-5.00pm የአማርኛ ቋንቋ ማንበብ: የአማርኛ ቋንቋ መፃፍ: የአማርኛ ቋንቋ መስማትና መናገርን ያካተተ ትምህርት ይሰጣል::
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርቱም ለጀማሪ የሀሁ ፊደል ትምህርት, ለመሀከለኛ የቃላት ምስረታ ትምህርት, የመጨረሻ የንባብ እና የዓረፍተ ነገር ትምህርት::
5.00pm-6.00pm የአብነት (የድቁና ) ትምህርት

ዘወትር እሁድ ከቅዱስ ቁርባን በኋላ ለሕፃናትና ወጣቶች በ3 የእድሜ ክፍል (ከ5 እስከ 7 ዓመት፣ ከ8 እስከ 12 ዓመት፣ ከ13 ዓመት በላይ) መንፈሳዊ እና የመዝሙር ትምህርት ይሰጣል።
10.00am-10.30am የመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት
10.30am-11.00am የመዝሙር ትምህርት

ዘወትር እሁድ ከሰንበት አገልግሎት በኋላ ማኅበረ ካህናት እና የሰንበት ት/ቤት መዘምራን የየሰንበቱን እና የየበአላቱን ወረቦት/መዝሙሮች የማኅበር ቀለም ይሰማሉ/ያጠናሉ::

ሰመር ኮርስ:- ከሰኞ እስከ አርብ ለሁለት ተከታታይ ሳምንት የሚቆይ ሰመር ኮርስ ሰለ መሰረታዊ የሀይማኖት (የዶግማ) ትምህርት ይሰጣል:: ተማሪዎቹም በሶስት የዕድሜ ክፍል (ከ5ዓመት እስከ 8 ዓመት፣ ከ9 ዓመት እስከ 12 ዓመት፣ እና ከ13 ዓመት በላይ) ተመድበዉ ትምህርቱ ሙሉ ለሙሉ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚሰጥ ፕሮግራም ነዉ::
በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ለሁለት ሳምንት የቆዬ (June 12 – June 23) የልጆች ሰመር ኮርስ (summer courses) በሰላም ተጠናቋል::

ሰመር ካምፕ:- በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ለህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶች ለአንድ ሳምንት የቆዬ የሰመር ካምፕ (ከJuly 17- July 21 ከጠሗት 9:00am – 2:30pm) ዝግጅ በጥሩ ውጤት እና በሰላም ተጠናቋል:: የሰመር ካምፑ የተለያዩ ልጆችን የሚያስተምሩ እና የሚያዝናኑ ዝግጅቶች ነበሩት::

የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ (field Trip):- በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ለታዳጊ ወጣቶች ከዶ/ር ሲራክ በተገኘ የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ እርዳታ ታዳጊዎችና ወጣቶችን ያሳተፈ የመዝናኛ አገልግሎት በ Valley Fair እንዲያገኙ ተደርጓል።

የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ (field Trip):- በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. ከዶ/ር ሲራክ በተገኘ የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ እርዳታ ህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶችን ያሳተፈ በበንከር የውሀ ዳርቻ (Bunker beach) የመዝናኛ እና የሽርሽር ጉዞ (field Trip) በደመቀ መልኩ ተጠናቋል::

በዚሁ በተጠናቀቀው በ፪ሺ፲፭ ዓ.ም. የቤዛ ኩሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የ27ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ በድምቀት ተከብሯል።

አዲሱ ዘመንም የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን:: በ፪ሺ፲፮ዓ.ም ቃለ እግዚአብሔር ለመማር፣ ንስሐ ለመግባት፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለመቀበል ያብቃን።

ለተጨማሪ ማብራሪያ ጥያቄ ካለዎት?
• ወ/ሮ ቀለም ደጀኔ 651-332-1544
• አቶ ጌታቸው ደበበ 651-366-1650
• ወ/ት ማህሌት ተፈራ 651-442-3738
• አቶ ይገርማል ፈጠነ 651-332-6098
• አቶ ዮሐንስ ከበደ 612-707-5212
• ወ/ት ማርታ 952-437-4312