ዝማሬ በመምህር ምሕረተአብ አሰፋ

0/0

ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በመምህር ምሕረተአብ አሰፋ

በሚኒያፖሊስ፣  ሴይንት ፖል እና አካባቢው ለምትኖሩ ምዕመናን በሙሉ

IMG_3978 IMG_3964በጉባኤው ላይ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የድሬደዋና የአካበቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ተገኝተው ቡራኬያቸውን ይሰጡናል ።

IMG_3975በኢትዮጵያ እና በመላው አለም በስባኪ ወንጌልነቱ ታላቅ ዝናና ያተረፈው ወንድማችን መምህር ምሕረተአብ አሰፋ ከፊታችን ኃሙስ ጀምሮ ታላቅ የወንጌል ዘር ሊዘራ ተዘጋጅቷል። ዕለቱም ጥቅምት 26 እና 27, 2008 ሐሙስ እና አርብ ከ400PM ጀምሮ (Nov 5 & 6) ሲሆን ቦታውም በMinnehaha Academy “3100 West River PKWY Minneapolis MN 55406″ ሚኒሶታም በወንጌል ስትናወጽ ታመሻለች – ወንጌል እንዳይሰበክ የሚቅበዘበዘው ዲያቢሎስም ድል ይመታል። ቅድስት እናታችን እመብርሃንም ከፈ ከፍ ትላለች። ታዲያ በዚህን ዕለት እንኳን መቅረት ማርፈድ ያስቆጫል። 

 

 

ቦታ
Minnehaha Academy
3100 West River PKWY
Minneapolis MN 55406

ከሚኒያፖሊስ
Lake Streetን ይዘው ወደ ሴይንት ፖል ሲጓዙ 46ኛው ጐዳና ላይ ወደ ቀኝ ታጥፈሁ አስከ 32ኛው መንገድ ይሁዱ፤ Minnehaha Academyን 46 እና 32 ላይ ያገኙታል

ከሴይንት ፖል
Lake Streetን ይዘው ወደ ሚኒያፖሊስ ሲጓዙ 46ኛው ጐዳና ላይ ወደ ግራ ታጥፈሁ አስከ 32ኛው መንገድ ይሁዱ፤ Minnehaha Academyን 46 እና 32 ላይ ያገኙታል

ብፅዕ አቡነ አትናቴዎስ እና መምህር ምሕረተአብ አሰፋ ጉዞ ወደ ደብረሰላም መድኃኔዓለም

AbuneAtnatios ብፅዕ አቡነ አትናቴዎስ እና መምህር ምሕረተአብ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ሽኝት ሲደረግላቸው የሚያሳይ ፎቶ ግራፍ

ታላቅ የምስራች

“እግዚአብሔር ስለእናንተ ይዋጋል እናንተም ዝም ትላላችሁ።” ዘጸ.14፥14

ሁሉንም ነገር በጊዜው የሚያከናውን የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ሆኖ አባታችን ብጹእ አቡነ አትናቴዎስ የደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሊባርኩንና ቃለ ምእዳን ሊሰጡን ለሁለተኛ ጊዜ በደብራችን ይገኛሉ። እንዲሁም መምህር ምሕረተአብ አሰፋ በቤተክርስቲያናችን ለመጀመርያ ጊዜ ተገኝተው ሰፊ የወንጌል አገልግሎት ሊሰጡን ከብጹእ አባታችን ጋር ከቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ ጉዟቸውን ጀምረዋል።
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድም ብጹእ አባታችን እና መምህር ምሕረተአብ ማክሰኞ ኦክቶበር 27/2015 ዓ.ም ከምሽቱ 6፡30PM ላይ በቤተክርስቲያናችን ደማቅ አቀባበል የሚደረግላቸው ስለሆነ ይህን መልእክት ያነበባችሁ የሚኒያፖሊስና አካባቢዋ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ሁላችሁም በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ከብጹእ አባታችን በረከትን እንድታገኙ ስንል ይህን አስደሳች ዜና በደስታ እናስተላልፋለን።
የመጀመርያ ቀን የወንጌል ትምሕርት መርሐግብርም የፊታችን ሐሙስ ኦክቶበር 29/2015 ዓ.ም ከቀኑ 4፡30PM ጀምሮ  በደብረሰላም መድኃኔዓለም  የኢ/ኦ/ተ/ቤ ክርስቲያን በመምህር ምሕረተአብ አሰፋ የሚሰጥ መሆኑን ከወዲሁ እናስውቃለን።
“እግዚአብሔር ተዋጊ ነው፤ ስሙም እግዚአብሔር ነው።”  ዘጸ 15፥ 3

የደመራ በዓል የፊታችን ቅዳሜ መስከረም 15 (September 26) በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።

Demeraቤተ ክርስቲያኗ የአውቶቡስ አገልግሎት ስለምታቀርብ መኪናዎትን ኬማርት የገበያ ማዕከል አቁመሁ በአቶቡሱ ፌለን ፓርክ ይምጡ፣ ዝግጁቱም  እንደተጠናቀቀ ወደ ኬማርት እንመልሶታለን።

መልካም የደመራ በዓል።

መኪና ማቆሚያ ቦታ
245 Maryland Ave
St. Paul MN 55117

 

ደብረ ታቦር በደብረሰላም

የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ – ሐምሌ 19, 2007

በሰሞነ ህማማት ያውም በፀሎተ ኃሙስ ማውገዝ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮት የጣሰና ኢቂኖናዊ ነው ተባለ

የቤተ ክርስቲያኗ ምዕመናን የመልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ስብከት በዲቪዲ ተባዝቶ ለወደፊትም ለታሪክ ማጣቀሻ ይረዳ ዘንድ አንዲቀርብላቸው በጠየቁት መሰረት ከእሁድ ነሐሴ 28 2007 ወይንም July 5, 2015 ጀምሮ ለደብሩ መዕመናን ያከፋፈልን ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ እውነታውን በአለም ላይ የተበተነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ይረዳው ዘንድ በደብሩ ድረ ገጽ፣ ፊስቡክ አካውንት አንዲሁም በሌሎች ድረ ገጾች እንለቃለን።

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳትሆን በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያዊነት የሚንጸባረቅባት የኃይማኖት ተቋም በመሆኗ፣ በዘር፣ በቋንቋ ፣ እንዲሁም በጐጥ ያልተከፋፈለች ስለነበረች በኃይማኖት ሽፋን ለረዥም አመታት አብሮ የኖረን ህዝብ በዕለተ ሆሳዕና ለምን ቀደሳችሁ ብሎ በካህናቱ ላይ በሰሞነ ህማማት ያውም በፀሎተ ኃሙስ በአባ ዘካሪያስ የተላለፈው ውግዘት የቤተክርስቲያንን አስተምህሮት የጣሰና ኢቂኖናዊ መሆኑን መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ፍትሃ ነጋስትን በማጣቀስ እስተምረዋል። በመቀጠልም በሰሞነ ህማማት እንኳን ውግዘት ማውገዝ ይቅርና ይፍቱህ መባል እንኳን በተከለከለበት ጊዜ ያውም በፀሎተ ሀሙስ ለካህናቱ የውግዘት ደብዳቤ መስጠት የቤክርስቲያንን ህግ የጣሰ፣ ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቅ፣ ወደፊትም የማይታይ መሆኑን ለተሰበሰበው ምዕመናን አስረድተዋል። የምስልና የድምጽ ዝርዝር መልዕክቱን ከቪዲዮው ይመልከቱ

በሰሞነ ህማማት የተላለፈው ውግዘት ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የጣሰ ነው ተባለ

የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትላንትናው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ንግስ ተጋባዥ እንግዳ መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ በተገኙበት በደመቀና ባማረ መልኩ ያከበረ ሲሆን፤ በዕለቱም በደብረ ሰላም ካህናት ላይ ለምን በዕለተ ሆሳዕና ቀደሳችሁ ፣ ለምን ህዝበ ክርስቲያኑን አሳልፋችሁ ለተኩላ አልሰጣችሁም በማለት በአባ ዘካርያስ የተላለፈው የሰሞነ ህማማት ውግዘት  ኢቀኖናዊ መሆኑን አስተምረዋል።

መልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ በመቀጠልም በሰሞነ ህማማት እንኳን ውግዘት ማውገዝ ይቅርና ይፍቱህ መባል እንኳን በተከለከለበት ጊዜ ያውም በፀሎተ ሀሙስ ለካህናቱ የውግዘት ደብዳቤ መስጠት የቤክርስቲያንን ህግ የጣሰ መሆኑን ለተሰበሰበው ምዕመናን አስረድተዋል። የምስልና የድምጽ እንዲሁም ዝርዝር ዘገባውን ይዘን እንመለሳለን።

cdlabelየቤተ ክርስቲያኗ ምዕመናን የመልአከ ምህረት ቆሞስ አባ ምህረት ዘውዴ ስብከት በዲቪዲ ተባዝቶ አንዲቀርብላቸው በጠየቁት መሰረት በትላንትናው ዕለት ማለትም እሁድ ነሐሴ 28 2007 ወይንም July 5, 2015 የመጀመሪያውን ዙር ያከፋፈልን ሲሆን በተከታታይ ሳምንታትም ሁሉም ምዕመን እስኪዳረስ ድረስ አቅርቦቱ የሚቀጥል መሆኑን በታላቅ አክብሮት እንገልፃለን።

                            የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 

የሚካኤል በዓለ ንግስና የምስጋና ቀን June 20 & 21, 2015

St_MichaelJune 20
ከ3 – 5PM የቅዱስ ሚካኤል ዋዜማ
ከ5 – 9PM የምስጋና ዝግጅት (ቸሩ አባታችን በMay 11, 2014 በቤቱ ስላቆየን)

June 21
ከ3AM – 7AM ማኅሌት
ከ7AM – 10AM ስርዓተ ቅዳሴ
ከ10 AM – 12PM  መዝሙር፣ ስብከተ ወንጌል፣ ስርዓተ ንግስ
መጥተሁ ከቅዱስ ሚካኤል በረከት ይካፈሉ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Candlelight Vigil and Prayer Services in State Capitol and DSMA

LibyaMartyersPrayer2
Click on the image for more pictures

ባለፈው ኃሙስ በእስቴት ካፒቶል በሊቢያ በሰማዕትነት ላለፉት፣ በደቡብ አፍሪካና በየመን በግፍ ለተገደሉት ወገኖቻችን አስር የእምነት ተቋማት መሪዎች በተገኙበት በሚኒሶታ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያኖች ተገኝተው የጸሎትና የሻማ ማብራት መርኃ ግብር የከወኑ ሲሆኑ ሁሉም የእምነት አባቶች ለህዝባችን አንድነት ለሀገራች ሰላምን ተመኝተዋል። እንዲሁም እሁድ በደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን በመቶዎች የሚቆጠሩ የቤ/ ክርስቲያኗ ምዕመናን በተገኙበት ከቅዳሴ በኃላ ፀሎተ ፍትኃት እና የጧፍ ማብራት መርኃ ግብር ተካሒዷል። ፀሎተ ፍትኃቱም እንደተጠናቀቀ በተደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ከ$20,000.00 በላይ ሊሰበሰብ ችሏል። ገንዘቡም በዓለም ዙሪያ በስቃይ ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያኖች መርጃ ይውላል።

የጸሎት አገልግሎት (Prayer Services)

Ethiopia

የፀሎተ ፍትኃት መርኃ ግብር በሊቢያ ለተሰውት ሰማዕታት

እሁድ April 26 2015 ከጠዋቱ 5AM  – 10 AM በፀሎትና በቅዳሴ

ከ10AM ጀምሮ በፀሎተ ፍትኃት ይታሰባሉ

 

ወቅታዊ መግለጫ:-       የሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሊቢያ  በሚገኙ የእምነታችን ተከታዮች ላይ ራሱን አይ ኤስ እያለ በሚጠራው አሸባሪ ቡድን የተፈጸመባቸውን ዘግናኝ እና አሳዛኝ ግድያ በጽኑ ታወግዛለች።  በቀደሙት ዘመናት አባቶቻችን ቅዱሳን ሰማእታት ስለ እምነታቸው ሲሉ፣ ስለ ክረስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለ ቤተክርስቲያን ሲሉ በአላውያን ነገሥታት እና አሕዛብ መከራን ተቀብለዋል፣በመጋዝ ተሰንጥቀዋል፣ በእሳት ተቃጥለዋል፣ በፈላ ውኃ ተቀቅለዋል። ደማቸውንም ስለመንግሥተ ሰማያት ሲሉ አፍስሰዋል። ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

ዳግመ ትንሳኤ

PalmSunday30የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ ቤተ ክርስቲያን ከሆሳዕናና ከመድኃኔዓለም ንግስ ጀምሮ ፣ በሰመነ ህማማት፣ በጸሎተ ሐሙስ፣ በስቅለትና ከትንሳኤው ዋዜማ ጀምሮ በጣም ብዙ ህዝብ በተገኘበት በዓላቱን በደመቀ መልኩ አክብሯል፤ እነሆ አሁንም ዳግመ ትንሳኤን ዘንድሮ ለመጀመሪያ ግዜ ከጠዋቱ 4AM ጀምሮ በማህሌት፣ በቅዳሴና በስብከተ ወንጌል ሊያከብር ስላሰበ እርሶም መጥተው የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

Easter 2015 Video (የትንሳኤ አገልግሎት ቪዲዮ)

ድንግል ሆይ በኃጢአት በፍትወት የተጸነስሽ አይደለሽም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!

እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ “መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው” ብሎ ልበ አምላክ ዳዊት በመዝሙሩ ስለዘመረላት፤ ዳግመኛም ቅዱስ ያሬድ “ማርያምሰ ተኀቱ  እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ- ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና በቅድስና በድንግልና ታበራለች)” Continue reading ድንግል ሆይ በኃጢአት በፍትወት የተጸነስሽ አይደለሽም

የትንሳኤ አገልግሎት

This will conclude our  live Streaming  for Easter, you may still able to view prerecorded Services.