የስባተኛው አመት የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ በሰላም ተጠናቀቀ!

የተከበራችሁ የቤተክርስትያናችን አባላት እና ቤተሰቦች በሙሉ፤

እንደወትሮው ሁሉ የሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባላት እና ቤተሰቦቻቸው አዲስ የቤተክርስቲያን ሕንፃ ለመገንባት የሚያስፈልገውን የገንዘብ ወጪ በከፊል ለመሸፈን ያስችል ዘንድ ከኪሳችን ከምናዋጣው በተጨማሪ በ2023 ዓ.ም. የበጎፈቃደኝነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ ላይ በዩኤስ ባንክ ስታዲየም እና በሚኔሶታ ስቴት ፌር ተስማርተን ነበር :: እንደምታስታውሱት ሁሉ የመጨረሻው የበጎአድራጎት የስራ ቀን የተጠናቀቀው ያለፈዉ ወር እሁድ December 31, 2023 በዩኤስ ባንክ ስታዲየም ውስጥ በተደረገው የቫይኪንግ እና የግሪን ቤይ ፓከርስ ቡድኖች ጨዋታ ቀን ነበር:: ይህን የስራ ዘርፍ ከጀመርን እነሆ ሰባት አመታትን አአስቆጥረናል! ስለሆነም ባለፈው አመት ውስጥ ስለተከናወኑት የበጎአአድራጎት ስራዎች እና ስለተስበስበው የገንዘብ መጠን ለግንዛቤ ይረዳል ተብሎ በበጎአድራጎት ስራ አስተባባሪዎቹ በኩል የተዘጋጀ አጭር ሪፖርት ከዚህ በታች ባለው መልኩ ቀርቧል::

በ2023 ዓ.ም. ስንት የበጎፈቃድ አገልግሎት ሰራ ቀኖች ነበሩ?

በአመቱ በጠቅላላው 27 የበጎፈቃድ አገልግሎት ሰራ ቀኖች ነበሩ:: እነሱም 11 የቫይኪንግ ጨዋታዎች  ፣ 10 በሚኒሶታ ስቴት ፌር የመክና ማቆሚያ ማስተናገድ ስራ እና 6 በዩእስ ባንክ ስታዲየም በተደረጉ የሙዚቃ ኮንስርቶች እና ሞንስተር ጃም ትእይንቶች ነበሩ:: በ2023 በተደረጉት ስራዎች አንድ የበጎአድራጎት የስራ ቀን በአማካይ ከ 7 እስክ 9 ሰአቶች ይፈጅ ነበር::

በ2023 ዓ.ም. የበጎፈቃድ አገልግሎት ሰራ ላይ ስንት አባላት ቤተስቦችና ወዳጆች ነበሩ?

በዚህ አመት በጠቅላላው 111 የደብራችን አባላት ቤተስቦችና ወዳጆች በበጎአድራጎት ሰራ ላይ ተስማርተው ነበር:: ከ 7-14 ቀኖች የስሩ 10 እባላት  ፣ ከ4-5 ቀኖች የሰሩ ሌሎች 10 እባላት  ፣ ከ 2-3 ቀኖች የስሩ 36 አ ባላት  ፣ እንዲሁም አንድ ቀን ብቻ የስሩ 55 አባላት ነበሩ::

የስሩበት ቀኖች ብዛት የስሩ አባላት ብዛት%
7 – 14109%
4 – 5109%
2 – 3 3632%
15550%
ጠቅላላ 111100%

በ2023 ዓ.ም. የበጎፈቃድ አገልግሎት ሰራ ላይ እነማን ነበሩ?

በ2023ዓ.ም በተደረገው የበጎአድራጎት ስራ ወቅት ከ4 እስከ 14 ቀኖች ያገለገሉ 20 አባላት ስም ዝርዝር እና የስሩባቸው ቀኖች ብዛት በሚከተለው ሰንጠረዥ ላይ ተቀምጧል:: በዚህ አመት ብቻ 14 የበጎአድራጎት የስራ ቀኖችን በመስራት ከፍተኛውን ደረጃ የወሰደው የፕሮግራሙ አስተባባሪ ዶ/ር አሻርግሬ አትሬ ነው::

አባል ስም የስሩበት ቀኖች ብዛት
ዶ/ር አሻግሬ አትሬ14
ወ/ሮ በስልፍዋ መንገሻ11
ወ/ሮ አባይነሽ ደበላ10
ዶ/ር ብርሀኑ በለጠ10
አቶ ዳንኤል ከህሉ9
ዶ/ር መስፍን ተስፋዬ ገባያው9
አቶ አለምሰገድ ተስፋዬ8
አቶ እሸቱ ባዱንጋ8
አቶ ኤልያስ ጥላሁን7
አቶ ግርማ መኮንን7
አቶ አማረ በርሄ5
አቶ አሸናፊ ቡልቶ5
አቶ ፀጋ በዛብህ5
አቶ አበራ በርጃ4
አቶ ደረጀ አለሙ4
አቶ ደረስ ገ /ጊዬርጊስ4
ወ/ሮ እጅጋየሁ ይርጉ4
አቶ ገዛኸኝ ዳምጤ4
ወ/ሮ ራሄል ባልቻ4
ወ/ሮ ትእግስት መለሴ4

በ2021ዓ.ም. ፣ በ2022 ዓ.ም.  እንዲሁም በ2023 ዓ.ም. የበጎአድራጎት ስራ የስሩትን አባላት ስም ዝርዝር እና የስሩባቸውን ቀኖች ብዛት ለማየት የሚከተለዉን ሊንክ ይጫኑ! https://mesfinbcc.pythonanywhere.com/

በ2023 ዓ.ም. የበጎአድራጎት ስራ ምን ያህል ገንዘብ ተስበስበ?

በዚህ 2023 ዓ.ም. በበጎአድራጎት ስራ ለቤተክርስቲያን ማስሪያ የተስበስበው $56,166 ነበር :: በዚህ አመት በበጎአድራጎት ስራ ያስገባነው የገንዘብ መጠን ካለፉት ሁለት አመታት ስርተን ካገኘነው ጋር ሲነጻጸር እጅግ ያንሳል:: ክዚህ በታች ያለው ግራፍ እንደሚያሳየው በ2022 ዓ.ም. $199,950 እና በ2021 ዓ.ም. $223,558 አስባስበን ነበር::

በሰባት አመታት የበጎአድራጎት ስራ ለቤተክርስቲያን ማስሪያ የተስበስበው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ስንት ደረስ?

እስከአሁን ድረስ ለቤተክርስቲያን ማስሪያ በበጎአድራጎት ስራ የተስበስበው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን $811,312 ነው:: ዝርዝሩ ከዚህ በታች ተቀምጧል::

እንደምታዉቁት ሁሉ ትልቁ ጉልበታችንና እቅማችን በሁሉም መስክ የተጠናከረ እና የተሳተፈ የአባላት ጥንካሬ ሲኖረን ነው:: ስለዚህም 2024ዓ.ም. ሁላችንም በምንችለው እውቀት ጊዜ ጉልበት እና ገንዘብ በመረባረብና በመደጋገፍ አዲሱን ቤተክርስትያን አስርተን ለመገኘት ያበቃን ዘንድ እንትጋ: : በዚህ አጋጣሚ ሁላችሁም እከአሁን እና ወደፊትም ለምታደርጉት ትብብርና እርዳታ ሁሉ በረከቱ ይብዛላችሁ::

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
January 30, 2024
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

የዘንድሮው የከተራ እና ጥምቀት በዓል አከባበር እና የሃያ ሰባት አመቱ ቤዛኩሉ

በዚህ አመት የከተራ እና ጥምቀት በዓላት  ቅዳሜ ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016) እና እሁድ ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111 በሚገኘው ቦታ እንደወትሮው በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል:: የዘንድሮውን የጥምቀት በአል አከባበር ደማቅ እና ልዩ ያደረገው ነገር ቢኖር የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ለመጀመሪያ ጊዜ በመሀከላችን ተገኝተው ቡራኬ መስጠታቸው እንዲሁም የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች በብዛት ሆኖ በመሳተፍና ያቀረቧቸው ልዩ ልዩ መዝሙራት እና ሌሎች መንፈሳዊ ዝግጅቶች በልዩ ሁኔታ የሚጠቀሱ ናቸው ::

በተለያዩ ምክንያቶች የበዓሉን አከባበር መርኃግብር በቦታው በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ ለመሆን ላልቻላችሁ ሁሉ ይጠቅማል በማለት የቤዛ ኩሉ ሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች የሚዲያ ዝግጅት ክፍል ያካፈለንን ፎቶግራፎች ከዚህ በታች አቅርበናል::

የደብራችንን ታላቅነት ባገናዘበ መልኩ የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶችም ላቀረቧቸው መዝሙራት ፣ ልዩ መንፈሳዊ እና ትምህርታዊ ዝግጅቶች በተጨማሪም ላሳያችሁት መልካም አርአያዊነት ተግባር እያመሰገንን የደከማችሁበት ሁሉ ስለተሳካላችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን:: በዚህ አጋጣሚም  በደብራችን ውስጥ ለሚከናወኑት የሰንበ ት/ቤትና የልጆች ፕሮግራም ተሳታፊዎች: ካህናት: ፕሮግራም መሪዎች: አስተማሪዎች እና ወላጆች ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን። በተጨማሪም የቤዛ ኩሉ የሰንበት ት/ቤት ታዳጊና ወጣቶች የሚዲያ ዝግጅት ክፍልን ለፎቶግራፎቹ እጅግ በጣም እናመሰግናለን::

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን
January 24, 2024
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ከተራ እና ለብርሀነ ጥምቀቱ በስላም አደረሳችሁ!

እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ከተራ እና ለብርሀነ ጥምቀቱ በስላም አደረሳችሁ እያለች የፊታችን ቅዳሜ ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016) ከቀኑ 3 ፒኤም ጀምሮ የከተራ ጉዞ ወደ 6202 Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111 ይደረጋል:: ቀጥሎም እሁድ ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) ከቀኑ 1 ኤኤም ጀምሮ በማህሌት: ከቀኑ 5 ኤኤም በቅዳሴ እና ቀጥሎም በታቦት ሽኝት የብርሀነ ጥምቀት በአልን በደመቀ ሁኔታ ቤተክርስቲያናችን ታከብራለች::

በእለቶቹም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

የጥምቀት በአል የሚከበርበት አድራሻ: 6202 Bloomington Road, Fort Snelling, St. Paul, MN 55111
ስለ ከተራ እና ጥምቀት አከባበር መርኃ ግብር የሚከተለዉን ይመልከቱ!

የጥምቀት ጾም (የጋድ ጾም) :- ጥር 10, 2016 (Friday Jan 19, 2024)
ከተራ :- ጥር 11, 2016 (Saturday Jan 20, 2016)
ጥምቀት :- ጥር 12, 2016 (Sunday Jan 21, 2016) / The Baptism of Christ (Epiphany).

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የአስተዳደር ቦርድ
January 14, 2024
Minneapolis, Minnesota, U.S.A.

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/

እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በስላም አደረሳችሁ!

በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በስላም አደረሳችሁ እያለች የፊታችን ቅዳሜ ታህሳስ 27, 2016 (Saturday January 6, 2024) ከቀኑ 5 ፒኤም ጀምሮ በማህሌት: ቀጥሎም ከምሽቱ 11 ፒኤም ጀምሮ በቅዳሴ የእየሱሰ ክርስቶስን የልደት በአል በደመቀ ሁኔታ ታከብራለች:: በእለቱም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ እና ከወዳጅ ጋር በመምጣት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታቀርባለች::

መቼ: ቅዳሜ ታህሳስ 27, 2016 ከ 5 ፒኤም ጀምሮ
When: Saturday January 6, 2014 from 5pm

ከዚህ በታች ያሉት ፎቶግራፎች የሚያሳዩት የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የ2016 ዓ.ም. የእየሱሰ ክርስቶስ የልደት በአልን በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያናችን ውስጥ ሲያከብሩ ነዉ::

የቤዛ ኵሉ ሰንበት ትምህርት ቤት በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ ከተመሰረተ 27 አመት አስቆጥሯል::

አድራሻችን: 4401 Minnehaha Avenue S., Minneapolis, MN 55406
ስልክ: (612) 721-1222
ኢሜይል: dsmachurch@gmail.com
ዌብሳይት: https://www.debreselam.net
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/Debreselameotc/